Showing posts with label በዐቢይ ጾም ስድስተኛ ቀን ላይ የተሰጠ ተግሣጽ. Show all posts
Showing posts with label በዐቢይ ጾም ስድስተኛ ቀን ላይ የተሰጠ ተግሣጽ. Show all posts

Saturday, March 12, 2016

በዐቢይ ጾም ስድስተኛ ቀን ላይ የተሰጠ ተግሣጽ



በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 03 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ይህ ተግሣጽ ሊቁ የኦሪት ዘፍጥረትን መጽሐፍ እየተረጎመላቸው ሳለ በዐቢይ ጾም ስድስተኛው ቀን ላይ በዚያ ሰዓት እንደ ትልቅ መዝናኛ ይቈጠር የነበረውን የፈረስ ግልቢያን ለማየት ጉባኤዉን ትተው ለሔዱ ምእመናን የሰጠው ተግሣጽ ነው፤ ልክ የዛሬ 1620 ዓመት መኾኑ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይህን ተግሣጽ በእኛ ዘመን ኾኖ ቢያስተላልፈው ኖሮ እኛ እንደ ትልቅ መዝናኛ የምናያቸውን እንደ እግር ኳስ፣ ፊልም፣ እና የመሳሰሉትን ሊጠቀም እንደሚችል ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ለማንኛውም እስኪ እያንዳንዳችን ከያለንበት ኹናቴ እያየን ተግሣጹን ለእኔ ብለን እናድምጠው፡፡ አሁን ወደ ሊቁ፡- 
(1) ዛሬም እንደተለመደው ትምህርታችንን እንድንቀጥል እፈልጋለሁ፡፡ ነገር ግን እያመነታሁ ነው፡- ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ከብቦኛል፤ ግራ ገብቶኛል፤ ውስጤ ታምሟል - ተስፋ መቁረጥ ብቻ አይደለም፤ እጅግ አዝኛለሁ፡፡ ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላውቅም፤ የጥርጣሬ ስሜት ውስጤን ልምሾ አድርጎታል፡፡ ዕለት ዕለት ከዲያብሎስ ግብር ትርቁ ዘንድ ስናስተምራችሁና ስንመክራችሁ እንዳልነበረ፥ እናንተ ግን ወደዚያ ዲያብሎሳዊ ግብር ጥርግ ብላችሁ ሔዳችሁ፡፡ ከቃለ እግዚአብሔር ይልቅ የፈረስ ግልቢያው ማረካችሁ፡፡ እስከ አሁን ድረስ በማስተምራችሁ ትምህርት ለውጥ ካላመጣችሁ ከዚህ በላይ ላስተምራችሁ የምችለው ምን ብዬ ነው? ከምንም በላይ ተስፋ እንድቆርጥባችሁና ብስጭቴ ጣራ እንዲነካ ያደረገው ደግሞ ይኸን ኹሉ እየመከርናችሁ እየዘከርናችሁ ሳለ ዐቢይ ጾሙን መናቃችሁና ራሳችሁን በዲያብሎስ መረብ ውስጥ መጣላችሁ ነው፡፡ የፈለገ ያህል ልቡናው እንደ ድንጋይ ቢጠነክር እንዴት በዐቢይ ጾም ውስጥ ሰው እንደዚህ ያደርጋል? እመኑኝ! በጣም አፍሬባችኋለሁ፤ እስከ አሁን ድረስ ያስተማርኩት ትምህርት ምንም ጥቅም እንዳላስገኘ በማየቴና ጭንጫ ላይ ስዘራ በመክረሜ በጣም አፍሬባችኋለሁ፡፡

FeedBurner FeedCount