Showing posts with label በዓለ ዕረፍቶሙ ለቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ. Show all posts
Showing posts with label በዓለ ዕረፍቶሙ ለቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ. Show all posts

Wednesday, July 11, 2012

በዓለ ዕረፍቶሙ ለቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ!


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
  ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በታናሽ ኤስያ እየዞረ በቃሉ እያስተማረ በመልእክትም እየጻፈ ምእመናን በሃይማኖት እንዲጸኑ በመከራም እንዲታገሱ እየመከረ ካጽናናቸው በኋላ በሮሜ ለክርስቶስ መስክሮ እግዚአብሔርን የሚያመሰግንበት ዘመኑ ሲደርስ በ67 ዓ.ም ወደ ሮሜ ገብቶ ያስተምር ጀመር፡፡

ኔሮን ቄሳርም በዚያ ዘመን በክርስቲያን ላይ የሚቃጠለው የቁጣ እሳት ገና አልበረደለትም ነበርና ቅዱስ ጴጥሮስን አሲዞ አሰረው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ግን በምሴተ ሐሙስ ጌታው በተያዘ ጊዜ ስለ ደረሰበት ፈተና ጌታዉን አላውቀዉም ብሎ መካዱ ብቻ ትዝ እያለው ያዝን ነበር እንጂበመታሰሩ አላዘነም ነበር፡፡…

ኔሮን ቄሳርም ቅዱስ ጴጥሮስን አሲዞ ካሰረው በኋላ ወደ አካይያ ዘምቶ ነበርና በዘመቻው ድል አድርጎና ደስ ብሎት ወደ ሮሜ ሲመለስ አረማውያን የሆኑ መኳንንቱን ደስ ለማሰኘትና አማልክቱን ለማክበር ሲል በቅዱስ ጴጥሮስና በሌሎችም ክርስቲያኖች ሁሉ የሞት ፍርድ ፈረደባቸው፡፡ የቅዱስ ጴጥሮስም ሞት በመስቀል እንዲሆን ታዘዘ፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስም በመስቀል ተሰቅሎ እንዲሞት መፈረዱን በሰማ ጊዜ ጌታችን ወአመሰ ልሕቅ ባዕድ ያቀንተከ ሐቄከ ወይወስደከ ሀበ ኢፈቀድከ ብሎ የነገረው ቃል ትዝ አለውና አላውቀውም ብዬ መካዴን ሳያስብብኝ በዚህ ፍጹም ይቅርታ ያደርግልኛል በማለት እጅግ ደስ አለው፡፡

የሚቀልበትም ሰዓት በደረሰ ጊዜ ከግዞት ቤት አውጥተው ሲወስዱት ከጌታዬ ከኢየሱስ ክርስቶስ እኩል እንዳልሆን ራሴን ወደ ታች ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ ብሎ ለመነ፡፡

በሮማውያን ሥርዓት ቅጣት የተፈረደበት ወንጀለኛ የሮሜ ተወላጅ የሆነ እንደሆነ የወንጀሉ ትልቅነት እየታየ ግርፋት ወይም ሞት ይፈረድበታል እንጂ በአንድ ወንጀል ሁለት ቅጣት አይፈረድበትም፡፡
የውጭ ሀገር ወንጀለኛ እንደሆነ ግን ቅጣቱ ግርፋት እንደሆነገርፈው እስራት ይጨምሩበታል፡፡ ቅጣቱ ሞት እንደሆነ ግን አስቀድመው ገርፈው በኋላ በመስቀል ወይም በሌላ መሣርያ ይገድሉታል፡፡…

ስለዚህ ቅዱስ ጴጥሮስንም እንደ ሥርዓታቸው አስቀድመው ገርፈው በኋላ ራሱን ወደ ታች እግሩን ወደ ላይ አድርገው ሰቅለው ገደሉት፡፡ የተሰቀለውም በሐምሌ 5 /68 ዓ.ም ነው፡፡

ከሞተም በኋላ መርቄሎስ የሚባለው ደቀ መዝሙሩ ከመስቀል አውርዶ እንደ ሀገሩ ልማድ ሬሳውን በወተትና በወይን አጥቦ ሽቱ ቀብቶ በነጭ ልብስ ገንዞ ማር በተመላ ሣጥን ውስጥ አግብቶ አሁን ዛሬ ቫቲካን በሚባለው ሥፍራ ቀበረው፡፡
በረከቱና ረድኤቱ አይለየን!
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ቅዱስ ጳውሎስና ኔሮን ቄሳር በማናቸውም ነገር የማይስማሙ አጥፊና ጠፊ ነበሩ፡፡ ኔሮን ቄሳር ክፉና ዐመጸኛ ነበር፤ ቅ/ጳውሎስ ግን ደግና ፈቃደኛ ነበር፡፡ ኔሮን ቄሳር ከሐዲና ጨለማ በቃኝ የማይልንፉግ የሰይጣን ማደርያ ነበር፤ ቅ/ጳውሎስ ግን ሃይማኖታዊና ብርሃን በቃኝ የሚል ቸር የመንፈስ ቅዱስ ማደርያ ነበር፡፡

እነዚህ ሁለቱ ተጻራሪዎች በተገናኙና በተያዩ ጊዜ አንዱ የአንዱን ነገር አያስተውለውም ነበር፡፡ ስለዚህ ቅ/ጳውሎስ ወደ ፍርድ ሸንጎ ከቀረበ በኋላ ይፈታ ወይም ይቀጣ ሳይባል ወደ ግዞት ቤት መለሱት፡፡

ነገር ግን በሮሜ ከተማ ቅ/ጳውሎስ አስቀድሞ ያሳመናቸው ክርስቲያኖች እየበዙ ትምህርታቸውም እየበዛ መሔዱ በቅ/ጳውሎስ ምክንያት መሆኑን ኔሮን ቄሳር ስለተረዳው ይልቁንም ከቤተ መንግሥቱ ሹሞች ወገን ብዙ ሰዎች በክርስቶስ ስለ አሳመነበት የቤሮን ቄሳር ቁጣው ተመለሰበትና ጳውሎስን እንደገና ወደ ፍርድ ሸንጎ አቅርቡት ብሎ

FeedBurner FeedCount