Showing posts with label አሮጌውን ሰው አስወግዱ. Show all posts
Showing posts with label አሮጌውን ሰው አስወግዱ. Show all posts

Thursday, September 6, 2012

አሮጌውን ሰው አስወግዱ


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

የዚህ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያኖች በአዲሱ ዓመት በክርስትና ሕይወታቸው እንዲያድጉ እንጂ በፊተኛ ኑሮአቸው እንዳይመላለሱ ከጨለማ ሥራ ጋርም እንዳይተባበሩ ለማሳሰብ ነው፡፡ ይህን ቃል የተናገረው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች በጻፈላቸው መልእክቱ ነው /ኤፌ.4፡23/፡፡ 

  ኤፌሶን በሮም መንግሥት ሥር ሆና ታናሽ እስያ በምትባል አውራጃ በኤጅያን ባሕር ዳር /በዛሬዋ ኢያዘሎክ-ቱርክ/ የምትገኝ ታላቅ የንግድ፣ የአምልኮና የወደብ ከተማ ነበረች፡፡ በከተማዋ አርጤምስ /በላቲኑ አጠራር- ዲያና/ ለምትባል አምላክ ትልቅ መቅደስ ታንጾ ነበር /ሐዋ.19፡24፡27/፡፡ የባሕር አሸዋ የድሮይቱን ከተማ ስለሸፈናት ዛሬ ሰው አይኖርባትም፡፡ 

   ምንም እንኳን ክርስትና ወደዚህች ከተማ የገባው በጵርስቅላና በአቂላ አማካኝነት ቢሆንም /ሐዋ.18፡18-19/ ቤተ ክርስቲያኒቱ በይፋ የተቋቋመችው ግን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሦስተኛው ጉዞው ወደዚህች ከተማ መጥቶ ለሦስት ዓመት ያህል ወንጌል ካስተማረና ብዙ ሕዝብም ወደ ክርስትና ከመለሰ በኋላ ነው /ሐዋ.19፡8-27፣ 20፡31/፡፡ 

የኤፌሶን ከተማ ጢሞቴዎስ ጵጵስና የተሾመባትና በሰማዕትነት ያረፈባት፤ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ሞትን ሳያይ የተሰወረባት፤ በኋላም በ431 ዓ.ም የንስጥሮስ ክሕደት በጉባኤ ተወግዞ የእመቤታችን ወላዲተ አምላክነት በይፋ የተመሰከረባት ከተማ ናት፡፡ 

ሐዋርያው መልእክቲቱን የጻፈላቸው ዋና ዓላማ አንደኛ የኤፌሶን ክርስቲያኖች ምንም እንኳን አሕዛብ ቢሆኑም ከእስራኤል ጋር አንድ ሆነው በክርስቶስ ጸጋ መዳናቸውንና ሰማያዊ ክብር ማግኘታቸውን አውቀው በእምነታቸው እንዲጠነክሩ ለማድረግ ሲሆን /ምዕ.1-3/ ሁለተኛው ደግሞ በክርስትና ሕይወታቸው እንዲያድጉ እንጂ በፊተኛ ኑሮአቸው እንዳይመላለሱ ከጨለማ ሥራ ጋርም እንዳይተባበሩ ለማሳሰብ ነው /ምዕ.4-5/፡፡ እኛም እግዚአብሔር እንደወደደና እንደፈቀደ በሁለተኛው ዓላማ ላይ በማተኰር እንማማራለን፡፡ ማስተዋሉን ያድለን!!

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ምዕራፍና ቁጥር “ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፤ በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፤ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ” ይላል /ኤፌ.4፡22-24/፡፡ 

   ምን ማለት ነው? አሮጌ ማለት ፊተኛ፣ የቀድሞ፣ የድሮ፣ የጥንት፣ ያረጀ ማለት ነው፡፡ ፊተኛ ኑሮ ማለትም የድሮ ባሕርይ፣ የቀድሞ ምልልስ ማለት ነው፡፡ የሰው ልጅ አሮጌነትን የተላበሰው በቀዳማዊ አዳም በደል ምክንያት ነው፡፡ ቀዳማዊ አዳም አስቀድሞ በእግዚአብሔር አርአያና አምሳል የተፈጠረ ንጽሐ ጠባይዕ ነበረው፡፡ መተዳደሪያውም ጽድቅ ብቻ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ይህን እስከ መጨረሻ መጠበቅ አልቻለም፡፡ ሐዋርያው እንደነገረን  ዲያብሎስ ከቅንአት የተነሣ /ጥበብ.1፡24/ በእባብ አካል ተሰውሮ አዳምን በሚያታልል ምኞት ተፈታተነው /ዘፍ.3፡1/፡፡ ወደ እርሱ ፈቃድ ስቦም “አትብሉ” የተባሉትን የዛፍ ፍሬ ከሚስቱ ጋር እንዲበላ አደረገው፡፡ ያን ጊዜ አዳም ከክብሩ ተዋረደ፡፡ አሮጌ ሆነ፡፡ ባሕርዩ ወደ ኃጢአት ያዘነበለ ሆነና በእርሱ ጠባይ

FeedBurner FeedCount