Showing posts with label አንዲት/አሐቲ/ ሰንበት ትምህርት ቤት. Show all posts
Showing posts with label አንዲት/አሐቲ/ ሰንበት ትምህርት ቤት. Show all posts

Friday, May 29, 2015

አንዲት/አሐቲ/ ሰንበት ትምህርት ቤት



በዲ/ን ሕሊና በለጠ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 21 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡-  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
አንድወይምአንዲትየሚለው ቃል በቤተ ክርስቲያናችን ከቁጥር መግለጫነቱ ባሻገር የጠለቀ ምሥጢራዊ ፍች ያለው ቃል ነው፡፡
ከምሥጢራት ሁሉ የረቀቀውን የሥላሴን ምሥጢር አባቶች ባስተማሩንና በተገለጠልን መጠን ስንገልጽ አንድምሦስትም መሆናቸውን እንመሰክራለን፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የምናመልከው አምላክ በባሕሪየ መለኮቱ አንድ እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስአንድ ጌታበማለት ይጠቁመናል፡፡ በእርሷ መንገድነት ካልሆነ በቀር ጌታን ማግኘት አይቻልምና ይሄ አንድ ጌታ የሚገኝባትን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና ሃይማኖትን መጽሐፍ ቅዱስአንድ ሃይማኖትሲል ይጠራታል፡፡ ያመነና የተጠመቀ ነውና የሚድነው /ማር.1616/ የድኅነት መንገድ ወደሆነችው ወደዚህች ሃይማኖት መግቢያ በር የሆነውን ምሥጢረ ጥምቀትንም በመቀጠልአንዲት ጥምቀትሲል ይገልጸዋል፡፡/ኤፌ.45/ ሐዋርያት ልቡናቸውና ቃላቸው በአንድነት የተባበረ ነውና በኤፌሶን መልእክቱ ቅዱስ ጳውሎስአንድያላትን ሃይማኖት ሐዋርያው ይሁዳምለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽማ የተሰጠችይላታል፡፡ /ይሁ. 3/

FeedBurner FeedCount