Showing posts with label እግዚአብሔር የተወሰኑ ሰዎችን ለመንግሥቱ ሌሎችን ደግሞ ለገሃነም ወስኗልን. Show all posts
Showing posts with label እግዚአብሔር የተወሰኑ ሰዎችን ለመንግሥቱ ሌሎችን ደግሞ ለገሃነም ወስኗልን. Show all posts

Tuesday, September 4, 2012

እግዚአብሔር የተወሰኑ ሰዎችን ለመንግሥቱ ሌሎችን ደግሞ ለገሃነም ወስኗልን?


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

አንዳንድ ወገኖች የሰው ዕድል ፈንታው ጽዋዕ ተርታው ከጻድቃን ወይም ከኩንኖች መሆን አስቀድሞ በእግዚአብሔር የተወሰነ ነው በማለት ይናገራሉ፡፡ ለዚህ ቅድመ ውሳኔ /Predestination/ ሐሳባቸውም አስረጅ አድርገው የሚያቀርቧቸው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅሶች አሏቸው /ሮሜ.911-21 ኤፌ.14/፡፡ ከዚህም በመነሣት ድኅነት የሚገኘው ከዘመናት በፊትእግዚአብሔር በወሰነው መሠረት እንጂ ሰው በሚፈጽመው ሥራ የማይሰጥ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ እስኪ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በዚህ ጉዳይ ምን ብላ እንደምታስተምርና የእነዚህ ሰዎች አስተምህሮ የሚያመጣው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ተፋልሶ ምን እንደሆነ እንመልከት!

             1.አስቀድሞ ሁሉን ማወቅ ወይስ አስቀድሞ መወሰን?
 እግዚአብሔር ዓለምን ከመፍጠሩ በፊት እስከ ዓለም ፍጻሜ ሊሆን ያለውን ነገር ምንም ሳይሰወርበት ሁሉን ያውቃል፡፡ አንድ ሰው ከቅዱሳን ወገን አልያም ከኃጥአን ወገን እንደሚሆን አስቀድሞ ያውቃል /ሮሜ.828-30/፡፡ ሆኖም ግን የተወሰኑትን ለመንግሥተ ሰማያት የተወሰኑትን ደግሞ ለገሃነም ለኩነኔ አልፈጠራቸውም፡፡ እንዲህ ቢሆንስ ኖሮ እግዚአብሔር አንድስ እንኳ ይጠፋ ዘንድ እንደማይፈልግ ባለተናገረ ነበር /2ጴጥ.39/ የዓለም ሕዝብ በሙሉ ለድኅነት መጥራት ባላስፈለገ ነበር /ማቴ.2819 ሮሜ.819/ ሰዎች ሁሉ ይድኑ እውነትንም ያውቋት ዘንድ ባልወደደ ነበር /1ጢሞ.24/፡፡ በመሆኑም ሰው ከእግዚአብሔር በተቀበለው ነጻ ፈቃዱ ተጠቅሞ ወይ ርትዕት በሆነች የሕይወት መንገድ ይጓዛል አሊያም የሞት መንገድ በምትሆን በኃጢአት መንገድ ይሄዳል፡፡ ድኅነት ለሁሉም የተሰጠ ቢሆንም የሰው ድኅነቱ በራሱ መሻትና የነጻ ፈቃድ ምርጫ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ሄሬኔዎስ የተባለ አባትም፡- ጥቂቶች በተፈጥሮ ክፉ ቢሆኑ ሌሎችም መልካም ቢሆኑ መልካሞቹ ስለ መልካምነታቸው መልካም ሠሩ ተብለው ምስጋና የተገባቸው አይሆኑም፡፡ ሲፈጠሩ እንዲህ ሆነው ነውና፡፡ ክፉዎቹም ስለ ክፋታቸው ነቀፌታን ባላገኛቸው ነበር፡፡ ጥንቱንም ሲፈጠሩ እንዲህ ሆነዋልና ብሏል /Iraneus, Book IV, Chap.37/፡፡ 

             2. እግዚአብሔር አያዳላም ፍርዱም ርቱዕ ነው!
 እግዚአብሔር የተወሰኑ ሰዎችን ለመንግሥተ ሰማያት ሌሎችን ደግሞ ለገሃነም አስቀድሞ ወስኗል ማለት ክብር ምስጋና ለስም አጠራሩ ይሁንና እግዚአብሔር ያዳላል እንደማለት ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ግን አምላካችሁ እግዚአብሔር የአማልክት አምላክ፣ የጌቶች ጌታ፣ ታላቅ አምላክ፣ ኃያልም፣ የሚያስፈራም፣ በፍርዱም የማያዳላ፣ መማለጃም የማይቀበል ነው /ዘዳ.1017/ እግዚአብሔር ለሰው ፊት እንደማያዳላ በእውነት አየሁ /ሐዋ.1034/ ከእግዚአብሔር ዋጋችሁን እንደምትቀበሉ ታውቃላችሁ፤ ለክርስቶስ ትገዛላችሁና፤ የሚበድል ግን ፍዳውን ያገኛል እርሱም አያደላለትም ይላል /ቈላ.323/፡፡  

           3.አስቀድሞ መወሰን አለ ከተባለ ትእዛዛት ለምን ተሰጡ?
 እግዚአብሔር የተወሰኑትን ሰዎች ለመንግሥተ ሰማያት የተወሰኑትን ደግሞ ለገሃነም ፈጠረ ከተባለ ሰዎች በአእምሮ ጠባይ መሪነት፣ በሥነ ፍጥረት አስተማሪነት፣ በሕገ ልቡና አዋቂነት መልካም ሥራ መሥራት

FeedBurner FeedCount