Showing posts with label ዕለተ ምጽአት. Show all posts
Showing posts with label ዕለተ ምጽአት. Show all posts

Saturday, April 2, 2016

ዕለተ ምጽአት



ምንጭ፡- ቅዳሴ አትናቴዎስ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 24 ቀን፣ 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ይህቺ ዕለት (ቅድስት ሰንበተ ክርስቲያን) በምትሠለጥንበት ጊዜ አዲስ ሥራ አዲስ ነገርም ይኾናል፡፡ ያን ጊዜ የፀሐይና የጨረቃ የከዋክብትም ብርሃን ወይም ፀዳል ወይም በጋ የለም፡፡
በውስጥዋ በነፍስ ሕያው ኾኖ የሚንቀሳቀስ ፍጥረት ሳይኖርባት ምድር ሰባት ቀን ታርፋለች፡፡ እንደ ረቂቅ ፉጨት ያለ ቃል ይላካል፡፡ በዚያችም ቃል የሰማያት ጽንዕ ይወገዳል፤ የምድር ግዘፍ ይነዋወጻል፡፡
ያን ጊዜ መቃብራት ይከፈታሉ፡፡ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የፈረሱ ሙታን ፈጥነው እንደ ዓይን ቅጽበት ይነሣሉ፡፡ አብ መንግሥቱንና ፍርዱን ለልጁ ይሰጣል፡፡ ግሩም የኾነ የነጐድጓድም ቃል ይሰማል፡፡ ከመጀመሪያው (ከጥንት) ጀምሮ ጆሮ ያልሰማው ዓይንም ያላየው!
የእሳት ክንፎች ያሏቸው ግሩማን መላእክት በፊቱ ይቆማሉ፡፡ ስም የሌላቸው፣ እገሌና እገሌ የማይሏቸው በአብ መጋረጃ ውስጥ የሚኖሩ ባለሟሎች መላእክት ናቸው፡፡ የሊህም ክንፍ ከክንፍ ጋር ይሳበቃል፤ ይሰማሉ፤ ያንጐደጕዳሉ፤ ሰይፋቸውንም ይመዛሉ፤ ጽናታቸውንም ያሳዩ ዘንድ ይበራሉ፡፡

FeedBurner FeedCount