Showing posts with label ዘወረደ ዘዐርብ. Show all posts
Showing posts with label ዘወረደ ዘዐርብ. Show all posts

Thursday, February 27, 2014

ዘወረደ ዘዐርብ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
 
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 21 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ
ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ 

 የጽዮን አምሳያ ለሆነችው ቤተክርስቲያን እንዲህ ይላል ቅዱስ አባት ዜመኛው ኢትዮጵያዊጎሕ ጎሐ ወኮነ ጽባሐ ንሳለማ ለጽዮን ምክሐ እምነ በሀ - ሌሊቱ ነጋ ጠዋትም ሆነ መመኪያችን እናታችን ጽዮን እንሳለማት፡፡” እኔም በቤተክርስቲያን ጡቶች ያደግሁ ከእርሷ በሚሆን ወተት ላደጉና ለኖሩ ምዕመናን እናታችን ለምትሆን ለቤተክርስቲያን ዜመኛው በሰጣት ሰላምታ የጽዮን ልጆች ሆይ ሰላም ለእናንተ ይሁን ሰላማችሁ ይብዛ፡፡ ትናንት በቅኔ ማሕሌት እንደተኛው ከበሮ (ከበሮ አገልግሎት በዚህ ወቅት አይሠጥም) ሳይሆን የድካም የሆነ ወዝ (ላብ) ከማይታይበት ከላይ ታች፣ ከግራ ቀኝ፣ ወደፊት ወደኋላ በሚለው መቋሚያ እየታገዝን ዜማውን በቤተክርስቲያን ስለቤተክርስቲያን ሠምተናል፡፡ ዛሬም እንዲሁ ስለ ቅድስት ቤተክርስቲያን (ጽዮን) እና ቅዱስ መስቀል በመሃልም መልካም ቃለ እግዚአብሔር እንሠማለን፣ የአባታችን አምላክ ከመላእክቱ ጋር ያሰልፈን፡፡

FeedBurner FeedCount