Showing posts with label የኢትዮጵያ የዘመን አቈጣጠር - ክፍል 1. Show all posts
Showing posts with label የኢትዮጵያ የዘመን አቈጣጠር - ክፍል 1. Show all posts

Tuesday, September 10, 2013

የኢትዮጵያ የዘመን አቈጣጠር - ክፍል 1

ገ/እግዚአብሔር ኪደ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ ጳጉሜን 5 ቀን፥ 2005 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

መግቢያ

  የሰው ልጅ ሕይወት ከጊዜ ጋር በእጅጉ የተቈራኘ ነው፡፡ እያንዳንዱ ማኅበረሰብም የራሱ የሆነና ይህን ከሕይወቱ ጋር የተቈራኘውን ጊዜ የሚቀምርበት የዘመን አቈጣጠር አለው፡፡ ሊቃውንት ሲናገሩ “ለቃለ እግዚአብሔር ጥናት ሰዋስው፥ ለምስጋና ዜማ፥ ለምሥጢራት ቀኖና እንደሚያስፈልግ ሁሉ ለጌታ በዓላትም ባሕረ ሐሳብ የግድ ያስፈልጋል” ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያም የራሷ የሆነ ሐሳበ ዘመን ማለትም የዘመን አቈጣጠር አላት፡፡ ይህ የዘመን አቈጣጠር (ሐሳበ ዘመን) የዘመናት፣ የዓመታት፣ የወራት፣ የሳምንታት፣ የዕለታት፣ የሰዓታት፣ የደቂቃዎች፣ የቅጽበትና (የካልዒትና) የመሳሰሉት ጊዜያት በሐሳብ የሚመዘኑበት፣ የሚሰፈሩበት፣ የሚቈጠሩበት ምድብና ቀመር ተሰጥቶአቸው የሚገኙበትን ውሳኔና ድንጋጌ እያሰማ የሚጠራበት ትምህርታዊ ውሳኔ ነው፡፡

FeedBurner FeedCount