Showing posts with label የኢትዮጵያ የዘመን አቈጣጠር - ክፍል 2. Show all posts
Showing posts with label የኢትዮጵያ የዘመን አቈጣጠር - ክፍል 2. Show all posts

Tuesday, September 10, 2013

የኢትዮጵያ የዘመን አቈጣጠር - ክፍል 2

ገ/እግዚአብሔር ኪደ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ መስከረም 1 ቀን፥ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ዐውደ ዓመት
  ዐውደ ዓመት ማለት በፀሐይ 365¼ ዕለት፥ በጨረቃ 354 ዕለት ነው፡፡ ከፀሐይ ወሮች ዐጽፈ አውራኅ፥ ከጨረቃ ወሮች ደግሞ ሕጸጸ አውራኅ ይገኛል፡፡ ዐጽፈ (ድርብ፣ ዕጥፍ) አውራኅ ማለት በየወሩ 30 ቀን በሱባኤ ሲቀመር (ለሰባት ሲከፈል) የሚቀረው 2 ቀን በሌላው ወር ተደምሮ የሚቈጠር ስለሆነ ነው፡፡ ጨረቃ በዕለት፣ በ15 ቀን፣ በወርና በዓመት የምታጐድለው ቀንና ሰዓት ሕጸጽ ይባላል፡፡ ለምሳሌ በፀሐይ አቈጣጠር አንድ ወር 30 ቀን ሲሆን በጨረቃ ግን አንዳንዴ 29 ይሆናል፡፡ ይህ ጨረቃ ከፀሐይ የምታጐድለው አንድ ቀን ነው ሕጸጽ እያልነው ያለነው፡፡ ስለዚህ በፀሐይ አቈጣጠር ዐዲስ ዓመት መስከረም 1 ሲሆን በጨረቃ አቈጣጠር ግን ነሐሴ 24 ወይም ነሐሴ 25 ይሆናል ማለት ነው፡፡ [ጨረቃ ለ6 ወራት 29፣ 29 ትሆናለች፡፡ ስለዚህ 6 ቀን ታጐድላለች ማለት ነው፡፡ 5 የጳጉሜንን ዕለታትንም ጨምራ ስታጐድል በጠቅላላ 11፥ በየአራት ዓመት ደግሞ 12 ቀናት ታጐላለች፡፡ በዚህም ምክንያት በጨረቃ አቈጣጠር ዐዲስ ዓመት ነሐሴ 24 ወይም በየአራት ዓመት ነሐሴ 25 ይሆናል ማለት ነው፡፡]

FeedBurner FeedCount