Showing posts with label የወልድ ፍቅር. Show all posts
Showing posts with label የወልድ ፍቅር. Show all posts

Wednesday, June 6, 2012

የወልድ ፍቅር!!


 
ባሕርይውን ዝቅ ብሎ የታየው ከሁላችንም በላይ ከዘመናት ሁሉ አስቀድሞ የነበረው ነው፤ ይህ ሰው የሆነው ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ውስጥ የሚኖረው ነው፡፡ የሆነው ሁሉ በእርሱ የተደረገ ነበር፤ የሆነው ሁሉ የተደረገው በምክንያት ነበር፡፡ ያለ ምክንያት የተደረገ አንዳችም ነገር የለም፡፡ እርሱም ለሰው ልጆች ዘላለማዊ ዋስትና ሲባል የተደረገ ነው፡፡ እርሱ ከመጀመርያው ያለ ምክንያት ነበር፡፡ ለእግዚአብሔር ሀልዎትስ ምን ምክንያት ይኖረዋል! ነገር ግን በምክንያት እርሱም የሰው ልጅን ወደ ቀደመ ክብሩ ለመመለስ ሥጋ ለብሶ ሰው ሆነ፤ የተፈጸመውም የእኛ ድኅነት ነው፡፡ያዋረድነውን እግዚአብሔርነቱን፣ የናቅነውን መንግሥቱን፣ ያቃለልነውን ወገኖቹ ሊያደርገን ስለዚህ የእኛ ባሕርይን ነሣ፡፡ ሥጋ ዝቅ ያለ ሲሆን እግዚአብሔርን ሆነ፡፡ እግዚአብሔርም የሰው ልጅ ሆነ፡፡በሥጋ ከድንግል ተወለደ፡፡ አስቀድሞ ግን ከባሕርይ አባቱ ከዘላለም የተወለደ የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ፡፡ ከሴት ተወለደ፤ ነገር ግን ድንግል ነበረች፡፡ የመጀመርያው ሰው ሁለተኛው መለኰት ነው፤ ሁለት ባሕርያት ያሉት አይደለም፡፡ በፍጹም ተዋሕዶ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ የሆነ እንጂ፡፡ ሰው እንደ መሆኑ አባት የለውም፤ አምላክ እንደ መሆኑ እናት የለውም፡፡ በማሕጸነ ድንግል ተወሰነ፤ በነብያቱ አፍ አምላክነቱ ተመሰከረለት፡፡ ነቢያቱ ብቻ የመሰከሩ አይደለም፤ አብም የምወደው ልጄ ነው አለ፤ እርሱም አባቴ ነው አለ እንጂ፡፡ ሰው እንደ መሆኑ በጨርቅ ተጠቀለለ፤ አምላክ እንደ መሆኑ የተገነዘበትን ጨርቅ ጥሎት ተነሣ፡፡ በበረት

FeedBurner FeedCount