Showing posts with label የውዳሴ ማርያም ትርጓሜ- መግቢያ. Show all posts
Showing posts with label የውዳሴ ማርያም ትርጓሜ- መግቢያ. Show all posts

Tuesday, August 6, 2013

የውዳሴ ማርያም ትርጓሜ- መግቢያ

ገ/እግዚአብሔር ኪደ
                                                                                  
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ ነሐሴ ፩ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም.)፡- ውዳሴ፡- “ወደሰ” ከሚል ግስ የወጣ ሲኾን ትርጓሜውም ማወደስ፣ መወደስ፣ አወዳደስ፣ ውደሳ፣ ምስጋና… ማለት ነው፡፡ “ውዳሴ ማርያም”        ሲልም የማርያም ምስጋና ማለት ነው፡፡
  የውዳሴ ማርያም መጽሐፍ ጸሐፊ ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም ሲኾን መጽሐፉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከጥንት ጀምሮ በጣም የታወቀና የተወደደ የጸሎት መጽሐፍ ነው። ይኸውም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በብዙ ምሳሌ እየመሰለ የሚያወድስ፣ ዘለአለማዊ ድንግልናዋን የሚያስተምር፣  በስነ ጽሑፋዊ ይዘቱም እጅግ ውብ የኾነ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ለማመስገን የተጻፈ ይኹን እንጂ በውስጡ እጅግ ረቂቅ የኾነ የስነ መለኮት ትምህርት (ለምሳሌ ስለ ምሥጢረ ሥላሴና ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ ) የያዘ መጽሐፍ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የቆሎ ተማሪዎች በቃል ትምህርቱ ዘርፍ ከየዘወትር ጸሎት ቀጥለው በንባብና በዜማ ይህን ውዳሴ ማርያም የተባለውን የትምህርት ክፍል ይማሩታል።
 ለጊዜው ይኸን እናቈየውና ወደ ተነሣንበት ዓላማ እንመለስ፡፡ በቀጥታ ወደ ትርጓሜው ከመግባታችን በፊትም ስለ ጸሐፊው ዜና መዋዕል በትንሹም ቢኾን በዚህ ክፍል ልናስቃኛችሁ ወድደናልና ተከታተሉን፡፡ መልካም ንባብ!

FeedBurner FeedCount