Showing posts with label የዐቢይ ጾምን መግባት ምክንያት በማድረግ የተሰጠ ትምህርት. Show all posts
Showing posts with label የዐቢይ ጾምን መግባት ምክንያት በማድረግ የተሰጠ ትምህርት. Show all posts

Sunday, March 6, 2016

የዐቢይ ጾምን መግባት ምክንያት በማድረግ የተሰጠ ትምህርት

በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 28 ቀን፣ 2008 ዓ.ም.)፤- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ይህ ትምህርት የተወሰደው የተወደደ መምህር ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ በ388 ዓ.ም. ዐቢይ ጾም መግቢያ ላይ ጀምሮት በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት መጨረሻ ላይ እየተረጎመ ከጨረሰው የኦሪት ዘፍጥረት መጽሐፍ ነው፡፡ ይህን ትምህርት ይከታተሉ የነበሩትን ምእመናን ከሊቁ አጠቃላይ ንግግር አንጻር ስናያቸውም የቤት እመቤቶችና በተለያየ የሙያ ሥራ የተሰማሩ ሠራተኞች ሲኾኑ የሚማሩትም በዐቢይ ጾም ምንም እኽል ሳይቀምሱ ነው፡፡   
(1) የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን እንደዚህ በልጆቿ ስትደምቅ እናንተም ጉባኤውን ለመታደም ደስ ብሏችሁ ተሰባስባችሁ ስትመጡ ዐይቼ ሐሴት አደረግሁኝ፤ ደስም አለኝ፡፡ ፊታችሁ እንዴት በደስታ እንደ ተመላ ስመለከት ጠቢቡልብ ደስ ሲለው ፊት ይበራልእንዳለው ልባችሁ ምን ያህል እንደ ተደሰተ ተገነዘብሁኝ /ምሳ.1513/፡፡ በመኾኑም፥ ዛሬ ማለዳ የተነሣሁት ከወትሮው በተለየ ትጋት ነው፡፡ ይኸውም ይህን መንፈሳዊ ደስታ ከእናንተ ጋር እንድካፈልና ቀጣዩ ወራት ቁስለ ነፍሳችሁ ድኅነት የሚያገኝበት ወርሐ መኾኑን አበሥራችሁ ዘንድ ነው፡፡ የኹላችንም ጌታ ልዑል እግዚአብሔር፥ ልክ እንደ ደግ አባት ባለፉት ወራት ለሠራነው ኃጢአት ሥርየት እናገኝበት ዘንድ ሽቶ መድኃኒት የሚኾን ቅዱስ ጾምን አዘጋጅቶልናልና፡፡

FeedBurner FeedCount