Showing posts with label የዮሐንስ ወንጌል የ22ኛ ሳምንት ጥናት. Show all posts
Showing posts with label የዮሐንስ ወንጌል የ22ኛ ሳምንት ጥናት. Show all posts

Monday, May 21, 2012

የገብረ ንጉሡ ልጅ መፈወስ- የዮሐንስ ወንጌል የ22ኛ ሳምንት ጥናት (ዮሐ.4፡43-ፍጻሜ)!!


  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!


“ከሁለቱ ቀኖችም በኋላ፣ ሳምራውያኑ ከእኛ ጋር ሁን ብለውት ለሁለት ቀናት ቃለ እግዚአብሔርን ሲያስተምራቸው ከቆየ በኋላ፣ እነርሱም የአይሁድ ወይም ደግሞ የሳምራውያን ብቻ ሳይሆን የዓለም ሁሉ መድኃኒት መሆኑን ካመኑና ለሴቲቱ ከነገሯት በኋላ ጌታችን ከዚያ ወጥቶ ወደ ገሊላ ሄደ” /ቁ.43/። ከተመቸን ብላችሁ በአንድ ቦታ አትኑሩ፤ ወጥታችሁ ወርዳችሁ አስተምሩ እንጂ ብሎ አብነት ለመሆን ከሰማርያ ወደ ገሊላ ሄደ /ወንጌል ቅዱስ አንድምታ ገጽ 476/፡፡ 


 ነገር ግን ብዙ ጊዜ ወደ ተመላለሰባት በኋላም አልቀበል ሲሉት “አንቺ ቅፍርናሆም እስከ ሰማይ ከፍ አልሽን? ወደ ሲዖል ትወርጃለሽ“ ብሎ ወደ ተናገረላት ወደ ቅፍርናሆም አልሄደም /ማቴ.11፡23/፤ ምክንያቱም “ነቢይ በገዛ አገሩ እንዳይከበር ኢየሱስ ራሱ መስክሮአልና” /ማቴ.13፡57/ /ቁ.44፣ ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ Homily On The Gospel of John Hom.35/።
 “ወደ ገሊላም በመጣ ጊዜ፥ የገሊላ ሰዎች ራሳቸው ደግሞ ለገቢረ በዓል ወጥቶ ሳለ በኢየሩሳሌም ያደረገውን ተአምራት ሁሉ አይተዋልና አመኑበት” /ቁ.45፣ ዮሐ.2፡23/። እነዚህ ገሊላውያን ምንም እንኳን እንደ ሳምራውያን ያለ ምልክት ባያምኑም ቃሉም ሰምተው ገቢረ ተአምራቱንም አይተው ካላመኑት የአይሁድ ሰዎች ግን ይሻላሉ /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒ ከማሁ/፡፡ 

FeedBurner FeedCount