Thursday, May 17, 2012

ካህናተ ደብተራ በዲ/ን ዳንኤል ክብረት=+=


«እናንተ ደብተራ ከምትባሉት በቀር ይህንን ሁሉ ያደረገ ማነው?ታመሰግኑታላችሁ፣ ታወድሱታላችሁ፣ እንዳንተ ያለ ኀያል ማነው? ትሉታላችሁ፤እንዳንተ ያለ ድል አድራጊ፣ እንዳንተስ ያለ ለጋሥ በሁሉ ዘንድ ወዴት አለ?እንዳንተ ያለስ ምጽዋት ሰጭ የት አለ? ትሉታላችሁ፡፡ እንዲህ ስታመሰግኑትምበኀጢአት ላይ ኀጢአትን ይጨምራል፡፡»
ይህንን ቃል ከዛሬ ሰባት መቶ ዓመታት በፊት የተናገረው ታላቁ ተጋዳይ አባት አባ በጸሎተሚካኤል ዘደብረ ጎል ነው፡፡ ንጉሥ ዓምደ ጽዮን ከክርስትና ሕግ ውጭ የአባቱን ሚስትበማግባቱ እንደ ዮሐንስ መጥምቅና እንደ ዮሐንስ አፈወርቅ ሳይፈራና ሳያፍር ፊት ለፊትበመገሠፁ ብዙ መከራ ደረሰበት፡፡ ተገረፈ፤ ታሠረ፤ ተሰደደም፡፡
አስቀድማ የንጉሡ ሚስት የነበረች በኋላ ደግሞ ንጉሡ ለአንዱ ወታደሩ የሰጣት አንዲት ሴትነበረች፡፡ ይህቺ ሴት ይህንን ሕይወት ንቃ ንስሐ ገባችና ሥጋወደሙ ተቀበለች፡፡ ንጉሥዓምደ ጽዮን «ሂዳችሁ አምጧት፤ እኔም በመኝታዬ አረክሳታለሁ» ብሎ በድፍረት ተናገረ፡፡መልክተኛ ወደ ሴቲቱ ሲሄድ እርሷ ወደ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ዘንድ ላከች፡፡

አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ልጆቹን እንዲህ አላቸው «ተነሡ እግዚአብሔር ሥራ እንዲሠራእንለምነው፡፡ ክውስጣዊ ልብሳችሁ በቀር ሌላውን አውልቁ፡፡ በፊቱም እያለቀስንእንለምነው»፡፡ ሌሊቱን ሙሉ በዕንባና በስግደት፣ በጸሎትና በማዕጠንት እግዚአብሔርንሲለምኑት አደሩ፡፡ ሲያለቅስ መሬቱ የሚረጥብ አለ፡፡ ሲሰግድ መሬቱ የሚጎደጉድ አለ፡፡ደረቱን ሲደቃ ውጭ ድረስ የሚሰማ አለ፡፡ ሲያጥን ዕንባው እሳቱን የሚያጠፋው አለ፡፡
ሌሊት ንጉሡ በከባድ ሕመም ታመመ፡፡ ነፍሱም ልትወጣ ደረሰች፡፡ ያን ጊዜ ባለሟሎቹቀረቡ፡፡ እርሱም «ይህ ሕመም በምን ምክንያት እንደ መጣ አውቄዋለሁ፤ ያቺን የበጸሎተሚካኤልን ልጅ ላረክሳት በመፈለጌ ነው፡፡ አሁንም ሂዱና ይቅር በለኝ በሉት» ብሎ በቤተመንግሥቱ የሚያገለግሉትን ካህናት ላካቸው፡፡
ካህናቱ ወደ አባ በጸሎተ ሚካኤል ሲደርሱ «ልጆቼ ተነሡ እግዚአብሔር ሰምቶናል፡፡ልብሶቻችሁን ልበሱ፤ መልክተኞችም መጥተዋል» አላቸው፡፡ እነርሱም ተነሥተው ከመቅደስሲወጡ የንጉሡን መልክተኞች አገኟቸው፡፡ መልክተኞቹም የንጉሡን መልክት ነገሩት፡፡ አባበጸሎተ ሚካኤልም «እግዚአ ብሔር ይቅር ይበልህ በሉት» አላቸው፡፡ የንጉሡን አገልጋይካህናት ግን እጅግ ወቀሳቸው፡፡
አባ በጸሎተ ሚካኤል የወቀሳቸው ካህናት በዚያ ዘመን «ካህናተ ደብተራ» ይባሉ ነበር፡፡ስማቸው የተወሰደው በንጉሡ ቤተ መንግሥት የምትገኘውንና በድንኳን ያለቺውን ቤተ ክርስቲያንስለሚያገለግሉ ነው፡፡ ነገሥታቱ በየሀገሩ ስለሚዘዋወሩ የድንኳን ቤተ ክርስቲያን ነበራቸው፡፡እዚያ ካህናት ይመደባሉ፡፡
የእነዚህ ካህናት ጠባይ በሌላው ቦታ ከነበሩት ካህናት ጠባይ ይለይ ነበር፡፡ ካህናተ ደብተራየሚታወቁባቸው ጠባያት ነበሯቸው፡፡ የመጀመርያው ጠባያቸው በገዳም ከሚኖሩት ቅዱሳንአበው ጋር አለመስማማታቸው ነው፡፡ ለእነርሱ ገዳማዊ ሕይወት ጊዜ ማጥፋትና ራስን ማሞኘትነው፡፡ በገዳም ያሉ አባቶቸንም በትኅትናቸው ምክንያት ይንቋቸው ነበር፡፡ እነርሱን ማሳጣትናመክሰስ ብሎም ከየገዳማቸው ማሳደድ የዘወትር ተግባራቸው ነበር፡፡ ገዳማቱ ሲፈቱና ማኅበረመነኮሳቱ ሲበተኑ ምንም ዓይነት ቁብ አይሰጣቸውም ነበር፡፡ እንዲያውም አንዳንድ ጊዜየንጉሡ ወታደሮች የሚያዝኑላቸውን ያህል ካህናተ ደብተራ ለገዳማውያን አባቶች አያዝኑም፡፡ ወደ ንጉሡ ዘንድ ደርሰው ጉዳያቸውን እንዳያስፈጽሙ ከጠባቂዎቹ ይልቅ የሚያስቸግሯቸውካህናተ ደብተራ ነበሩ፡፡
ሁለተኛው ጠባያቸው ደግሞ ማንኛውንም ነገር ከጥቅም ጋር ማገናኘታቸው ነው፡፡ የቤተክርስቲያን ሥርዓትና ሕግ፣ የእግዚአብሔር ቁጣና ቅጣት አይታያቸውም፡፡ ከንጉሡ ማዕድእየበሉና ፍርፋሪ እየለቀሙ፣ በንጉሡም ካባና ላንቃ እየተሸለሙ ስለሚኖሩ የሚሠሩትየሚገባቸውን ሳይሆን የሚያበላቸውን ነው፡፡ በቤተ መንግሥቱ ያገኙትን ክብርና ማዕድዳያጡ ሲሉ ማንኛውንም  ሃይማኖታዊ የሆነ ተግባር ከማድረግ አይመለሱም፡፡
በገድለ አቡነ ፊልጶስ ዘደብረ ሊባኖስ ላይ እንደ ተጻፈው ዓምደ ጽዮንንም ሆነ ልጁን ሰይፈአርእድን ትክክል ያልሆነ ትምህርት አስተምረው ያሳሳቱት ካህናተ ደብተራ ናቸው፡፡ አቡነፊልጶስ ዘደብረ ሊባኖስ ወደ ዓምደ ጽዮን ገብተው ለምን ይህንን ጥፋት እንዳጠፋና የአባቱንሚስት እንዳገባ ሲጠይቁት « ዐዋቂዎች የሆኑ ካህናት እርሷን ካላገባህ መንግሥትህ አይጸናምብለውኝ ነው» ነበር ያላቸው፡፡ ከካህናተ ደብተራ አንዱ የነበረው እወደድ ባዩ ዘአማኑኤልየተባለ ሰው ከንጉሥ ዓምደ ጽዮን በኋላ የነገሠውን ሰይፈ አርእድን በተመሳሳይ ስሕተትአሳስቶት ነበር፡፡ «ከጥቂት ጊዜም በኋላ ዘአማኑኤል የሚባል አንድ ሰው ተነሣ፡፡ ይህምበግብር ሳይሆን በስም ነው፤ እርሱ ንጉሡን እንዲህ ሲል አሳስቶታልና፡ አንተ ንጉሥ ነህናበአንዲት ሚስት ልትኖር አይቻልህም፤ ንጉሥማ ሦስት ሚስት እንዲያገባ ታዝዞለታል ብሎምአስተማረው» (ገድለ አቡነ ፊልጶስ፣ ገጽ 225)
ካህናተ ደብተራ ንጉሡን የሚያስደስትና ጥቅማቸውን የሚያስከብር ከመሰላቸው ከንጉሡ በላይምሄደው ግፍ ከመፈጸም አይመለሱም ነበር፡፡ በሰይፈ አርእድ ዘመነ መንግሥት ተመሳሳይስሕተት መሠራቱን አይተው አበው ከየአቅጣጫው መጥተው ሲገሥፁት አቡነ አኖሬዎስ ንጉሡንበኃይል ተናገረው፡፡ ይህንን ያየው የንጉሡ ማዕድ ባራኪ ካህን ወይም ቄስ ሐፄ ከወታደሮቹተሽቀዳደመና አቡነ አሮንን በጥፊ መታው፡፡ ለምን እንደ መታው ገድለ አቡነ አኖሬዎስ ሲናገር«በንጉሡ ዘንድ ሊመሰገን ሽቶ» ይለዋል፡፡ ያን ጊዜም አቡነ አኖሬዎስ «ለምን ትመታኛለህ?ለሰው ከማድላት ለእግዚአብሔር ማድላት አይሻልህም ነበር አለው ይላል፡፡ ቄስ ሐፄው ግንያሰበውን ምስጋና አላገኘም፡፡ በአበው ኀዘን ምክንያት ወዲያውኑ ሞተ፡፡
የካህናተ ደብተራ ሌላው ጠባይ ደግሞ ወተቱን ማጥቆር ከሉን ማንጣት ነው፡፡ እውነትንየሚመዝኗት ከጥቅማቸው አንፃር ብቻ ስለነበረ ኃጢአት ሲሠራ እያዩ ጽድቅ ነው፤ ግፍሲፈጸም እያዩ ቅድስና ነው ማለት ይወዱ ነበር፡፡ ነገሥታቱና መኳንንቱ በበደል ላይ በደልእንዲጨምሩ ያደርጓቸው የነበሩትም እነርሱ ናቸው፡፡ ለዚህ ነው አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ወደእርሱ ለማማለድ የመጡትን ካህናተ ደብተራ «እናንተ ደብተራ ከምትባሉት በቀር ይህንን ሁሉያደረገ ማነው? ታመሰግኑታላችሁ፣ ታወድሱታላችሁ፣ እንዳንተ ያለ ኀያል ማነው?ትሉታላችሁ፤ እንዳንተ ያለ ድል አድራጊ፣ እንዳንተስ ያለ ለጋሥ በሁሉ ዘንድ ወዴት አለ)እንዳንተ ያለስ ምጽዋት ሰጭ የት አለ? ትሉታላችሁ፡፡ እንዲህ ስታመሰግኑትም በኀጢአት ላይኀጢአትን ይጨምራል፡፡» ያላቸው በዚህ ምክንያት ነው፡፡
አንዳንዶቹ የካህናተ ደብተራ ወገኖች ሹመት እንጂ እምነት አልነበራቸውም፡፡ በገድለ አቡነአኖሬዎስ ላይ እንደ ግብጦን በተባለ ቦታ ንቡረ እድነት የተሾመ አንድ የካህናተ ደብተራ ወገንነበረ፡፡ ይህ ሰው ምንም ሳያደርገው በቅድስናው ብቻ አቡነ አኖሬዎስን ይጠላው ነበር፡፡
አንድ ቀን «ምን እንደምትሠራ ለማየት እመጣለሁ» ሲል ላከበት፡፡ ይህ ሰው ሹመት ሽልማትፈልጎ ንቡረ እድ ሆነ እንጂ እግዚአብሔርን እንኳን የማያመልክ ሰው ነበረ፡፡ ገድለ አቡነአኖሬዎስ እንዲህ ይላል «ቅዱሱም በዚያ በገዳሙ እያለ ስሙ ጳውሎስ የሚባል አንድ ሰውበትዕቢት «መጥቼ ሥራህን አያለሁ» ብሎ ወደ እርሱ ላከበት፡፡ ያም በስም መነኩሴና ንቡረእድ የሆነ፣ ከንጉሡም ዘንድ የተሾመ ነበረ፡፡ እርሱም ቤተ ክርስቲያንን አጠፋት፡፡ምእመናንንም አሳዘናቸው፡፡ የተላከውም መልክተኛ ለአባታችን ይህንን ነገረው፡፡ አባታችንምይህንን ሰምቶ «ኃጥእን እንደ አርዘ ሊባኖስ ከፍ ከፍ ብሎ አየሁት፤» ብሎ ተናገረ፡፡ ወደእግዚአብሔርም ስለ እርሱ ጮኸ፡፡ ያም በትዕቢቱ ሞትን አገኘ፡፡ ለቅዱሱም እንደ ሞተነገሩት፡፡ እርሱም «በተመለስኩ ጊዜ ግን አጣሁት» አለ፡፡ እርሱም «በምን ሞተአላቸው፡፡ እነርሱም «ሌሎች አማልክትን ያመልክ ነበር» አሉት፡፡ ቅዱስ አባታችንም መራርልቅሶን አለቀሰ፡፡ «ፈለግኩ ቦታውንም አላገኘሁትም» አለ፡፡
አንዳንዶቹ ካህናተ ደብተራ ክህነትን ለእንጀራ ማግኛና ለክብር መሸመቻ እንጂ አምነውበትየሚያገለግሉበት አልነበረም፡፡ ርስት ጉልት ስላለ፣ በንጉሡ ማዕድ ለመቅረብ ስለሚያስችል፣ልብስና መዓርግም ስለሚያሰጥ ነበር ወደ ክህነቱ የገቡት፡፡
ካህናተ ደብተራ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ለእንጀራና ክብር ማግኛ ብቻ እንጂ ለድኅነትስለማይ ጠቀሙበት አንዳንድ ጊዜ ነገሥታቱን ከአምልኮ እግዚአብሔር ወደ ጥንቆላ ይከቷቸውየነበሩት እነርሱ ነበሩ፡፡ በዐፄ ዳዊት ዘመን አባ ጊዮርጊስ ሲከራከራቸው የነበሩትና በኋላምበንጽሕናው ምክንያት ተመቅ ኝተው ወደ ዳሞት እንዲጋዝ ያደረጉት በጥንቆላ ሥራ ተሠማርተውየነበሩት ካህናተ ደብተራ ነበሩ፡፡
ካህናተ ደብተራ በዕውቀትና በቅድስና የሚበልጧቸውን አባቶችና ሊቃውንት አይወዷቸውም፡፡ቤተ ክርስቲያንን ለማበልጸግ፤ ለማደራጀትና ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት የሚጥር ሁሉጠላታቸው ነው፡፡ ግብጻዊው ጳጳስ አቡነ ያዕቆብ አቡነ ፊልጶስን ኤጲስ ቆጶስነት ሊሾመው ሲነሣበዋናነት የተቃወሙት ካህናተ ደብተራ እንደነበሩ ገድለ አቡነ ፊልጶስ ይነግረናል «እንደዚህአታድርግ፤ በአንድ ሀገር ሁለት ኤጲስ ቆጶስ ይሆናልን? ሕዝቡ ይከፋፈላል፤ የአንተም ክብርህይጠፋል፤ ምድረ ሼዋኮ ከፊል መንግሥት ናት፤ እንዴት እንደዚህ ትላለህ? ከኛ በኋላየሚመጣ ትውልድም ይህንን አይፈቅድም፤ ከኛም አስቀድሞ እንዲሁ ነበረ፡፡ እኛስ ከኛበፊት የነበሩ አበው ጳጳሳት ያላደረጉትምን አናደርግም፣ አንናገርምም» (ገድለ አቡነ ፊልጶስ፣ገጽ 197)
በወቅቱ የነበረውን የደቡቡን ክፍል ከአሥራ ሁለት ከፍሎ አሥራ ሁለት ወንጌላውያንን የሾመውንበሰሜኑ ክፍልም ሐዋርያትን ያሠማራውን ግብፃዊውን አቡነ ያዕቆብን ካህናተ ደብተራአልወደዱትም፡፡ የስብከተ ወንጌል መስፋፋትና የሕዝቡ ማወቅ ለእነርሱ የግብዝነትናየኃጢአት ሥራ ዕንቅፋት ይሆናል ብለው አሰቡ፡፡ በዚህም የተነሣ ይህንን የስብከተ ወንጌልአደረጃጀትና ሥምሪት ማጥፋት እንዳለባቸው ወሰኑ፡፡ በዚህም ምክንያት ዘአማኑኤል ንጉሡአቡነ ያዕቆብን ወደ ግብጽ እንዲመልሰው መከረው፡፡ አቡነ ያዕቆብ ስላወገዘውም በለምጽተመትቶ ሞተ፡፡ አቡነ ያዕቆብም ወደ ግብጽ ተመለሰ፡፡
በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ የእውነተኞቹ አባው፣ ሊቃውንትና ካህናት አገልግሎትና ትሩፋትለቤተ ክርስቲያን ብልጽግና እንዳይሰጥ ሲያሰናክሉና ለእውነት ዕንቅፋት ሲሆኑ የኖሩት ካህናተደብተራ ናቸው፡፡ እንክርዳዱ ከስንዴው ጋር አብሮ እስከ መከር ይኖራልና የካህናተ ደብተራጠባይና አሠራር ዛሬም ቤተ ክርስቲያንን ሲያውካት ይኖራል፡፡ እንደ አቡነ አሮን፣ እንደ አቡነበጸሎተ ሚካኤል እንደ አቡነ ፊልጶስና እንደ አቡነ አኖሬዎስ ያሉ ጀግኖችን እስክታገኝድረስ::  
(Source: danielkibret.com)

HOW IS IT THAT JESUS CHRIST MAKETH INTERCESSION FOR US? =+=


 IN THE NAME OF THE FATHER, THE SON, AND OF THE HOLY SPIRIT ONE GOD AMEN!
 
A lot of Reformers here in Ethiopia and other Sister Churches used to misinterpret this verse of the Apostle Paul in Hebrews 7:25 & Rome 8:34. But what does it mean in its Orthodox meaning? What does the Ancient Fathers say about it? Let’s hear its interpretation from one of our Oriental Orthodox Holy Fathers, St. John Chrysostom, the Arch Bishop of Constantinople and liveth from 347-407 AD.   

For as there were many a, because they were mortal, so [here is] The One, because He is immortal. “By so much was Jesus made a surety of a better covenant,” inasmuch as He sware to Him that He should always be [Priest]; which He would not have done, if He were not living. “Wherefore He is able also to save them to the uttermost, that come unto God by Him, seeing He ever liveth to make intercession for them.” Thou seest that he says this in respect of that which is according to the flesh. For when He [appears] as Priest, then He also intercedes. Wherefore also when Paul says, “who also maketh intercession for us” ( Rom. viii. 34 ), he hints the same thing; the High Priest maketh intercession. We have clearly seen this when Our Lord was saying ‘’Father, forgive them; for they know not what they do’’ (Luk.23:34).

 The question is that for He “that raiseth the dead as He will, and quickeneth them,” ( John v. 21 ), and that “even as the Father” [doth], how [is it that] when there is need to save, He “maketh intercession”? ( John v. 22.) He that hath “all judgment,” how [is it that] He “maketh intercession”? He that “sendeth His angels” ( Matt. xiii. 41, 42 ), that they may “cast” some into “the furnace,” and save others, how [is it that] He “maketh intercession”? Wherefore (the Apostle says) “He is able also to save.” For this cause then He saves, because He dies not. Inasmuch as “He ever liveth,” He hath (he means) no successor: And if He have no successor, He is able to aid all men. For there [under the Law] indeed, the High Priest although he were worthy of admiration during the time in which he was [High Priest] (as Samuel for instance, and any other such), but, after this, no longer; for they were dead. But here it is not so, but “He” saves “to the uttermost.” What is “to the uttermost”? He hints at some mystery which is the Holy Eucharist. Not on the day of the Good Friday only (the Apostle says) but there also He saves them that “come unto God by Him” through confession and this Holy Communion. If you asketh How does He save? I say unto you “In that He ever liveth” (the Apostle says) “to make intercession for them.” Thou seest the humiliation? Thou seest the manhood? For he says not, that He obtained this, by making intercession once for all, but continually, and when so ever it may be needful to intercede for them.

“To the uttermost.” What is it? Not for a time only, but there also in the future life. ‘DOES HE TEHEN ALWAYS NEED TO PRAY? Yet how can [this] be reasonable? Even righteous men have oftentimes accomplished all by one entreaty, and is He always praying? NO! If He need to pray always why then is He throned with [the Father]?’ Thou seest that it is a  condescension. The meaning is: Be not afraid, nor say, Yea, He loves us indeed, and He has confidence towards the Father, but He cannot live always. For He doth live always. “For such an High Priest also became us, who is holy, harmless, undefiled, separate from the sinners.” Thou seest that the whole is said with reference to the manhood. (But when I say ‘the manhood,’ I mean [the manhood] having Godhead; not dividing [one from the other], but leaving [you] to suppose what is suitable.) Didst thou mark the difference of the High Priest? He has summed up what was said before, “in all points tempted like as we are yet without sin.” (Heb. iv. 15.) “For” (the Apostle says) “such an High Priest also became us, who is holy, harmless.”

“Harmless”: what is it? Without wickedness: that which another Prophet says: “guile was not found in His mouth” ( Isa. liii. 9 ), that is, [He is] not crafty. Could anyone say this concerning God? And is one not ashamed to say that God is not crafty, nor deceitful? Concerning Him, however, in respect of the Flesh, it might be reasonable [to say it]. “Holy, undefiled.” This too would anyone say concerning God? For has He a nature capable of defilement? “Separate from sinners.” Does then this alone show the difference, or does the sacrifice itself also? How? “He needeth not” (he says) “daily, as the High Priest,  to offer up sacrifices for his sins, for this He did once for all, when He offered up Himself” ( Heb.7: 27) .“This,” what? Here what follows sounds a prelude concerning the exceeding greatness of the spiritual sacrifice and the interval [between them]. He has mentioned the point of the priest; he has mentioned that of the faith; he has mentioned that of the Covenant; not entirely indeed, still he has mentioned it. In this place what follows is a prelude concerning the sacrifice itself through the Holy Eucharist. 

 Do not then, having heard that He is a priest, suppose that He is always executing the priest’s office. For He executed it once, and thenceforward “sat down.” ( Heb. x. 12.) Lest thou suppose that He is standing on high, and is a minister, he shows that the matter is [part] of a dispensation [or economy]. For as He became a servant, so also [He became] a Priest and a Minister. But as after becoming a servant, He did not continue a servant, so also, having become a Minister, He did not continue a Minister. For it belongs not to a minister to sit, but to stand.

Glory be to God Amen!

( Source:-
1.St. John Chrysostom: Homily on the Epistle of Hebrews, Homily 13:6-9, English Version).
2.ድርሳን ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 13123-191(Dirsan zekidus Yohans Afewerk)- which is the Ethiopic Version of the above reference.)



Wednesday, May 16, 2012

ስለ ብርሃን እንዲመሰክር ስለ ተላከው መብራት (የዮሐንስ ወንጌል የሦስተኛው ሳምንት ጥናት)!

(ቢቻልዎት አስቀድመው ይጸልዩና በተመስጦ ሆነው ያንቡት)!
“ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ ሁሉ በእርሱ በኩል እንዲያምኑ ይህ ስለ ብርሃን ይመሰክር ዘንድ ለምስክር መጣ። ስለ ብርሃን ሊመሰክር መጣ እንጂ፥ እርሱ ብርሃን አልነበረም። ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም ይመጣ ነበር።” ዮሐ.1፡6-9
 አካላዊ ቃል ከአባቱ ዕሪና ሳይለይ ሰው ሆኖ ተገልጧልና ስለዚሁ ድንቅ ነገር ይመሰክር ዘንድ መልአክ ሳይሆን ዮሐንስ የሚባል ሰው ተላከ /አውግስጢኖስ/፡፡ ሌሎች ነብያት ክርስቶስ “ይወርዳል ይወለዳል” ብለው ትንቢት ቢናገሩም ክርስቶስን ሊያዩት ወደዱ እንጂ አላዩትም /ማቴ.13፡16-17/፤ ሐዋርያትም “ወረደ ተወለደ” ብለው አስተማሩ እንጂ “ከእኛ በኋላ ይመጣል” አላሉም /ሐዋ.4፡2/፡፡ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከእርሱ የሚበልጥ የሌለ መጥምቁ ዮሐንስ ግን እንደ ነብይ “ከእኔ በኋላ ይመጣል”፤ እንደ ሐዋርያም “ይመጣል ያልኳችሁ እርሱ ነው” እያለ ያስተምር ነበር /ዮሐ.1፡15፣30፣ ሄሬኔዎስ/፡፡ ወንጌላዊው ስለ አካላዊ ቃል ቀዳማዊነት እየመሰከረልን ቆይቶ አሁን ደግሞ ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ምስክርነት ጨምሮ የሚነግረን ምስክርነት በሁለት ወይም በሦስት ስለሚጸና ነው /ዘዳ.19:15፣ ቅ.ቄርሎስ/፡፡
 መጥምቁ ዮሐንስ ስለ ክርስቶስ የመሰከረው ምስክርነት እውነተኛው ብርሃን የሰው ምስክርነት አስፈልጐት ሳይሆን ሰዎች ስለ ብርሃን በሚረዱትና እነርሱን በሚመስል አገልጋይ (ዕሩቅ ብእሲ) ሲነገራቸው አምነው እንዲድኑ ስለተፈለገ ብቻ ነው /ዮሐ.5፡34፣ ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ/፡፡ በእርግጥም ዮሐንስ ሲመሰክርለት የነበረው ብርሃን ዓለም (የሰው ልጅ) በመላ አጥቶት የነበረ ብርሃን ነው /ኢሳ.9፡2፣ አርጌንስ/፡፡ አዎ! ዮሐንስ ከአማናዊው ብርሃን የተነሣ የሚያበራ መብራት ነበር እንጂ እርሱ ራሱ ብርሃን አልነበረም /ዮሐ.5፡35/፤ አማናዊው ብርሃንስ በመስቀል ላይ የዓለምን ጨለማ ያስወገደው የእግዚአብሔር በግ ነው /ኤፌ.2፡13-17፣ አውግስጢኖስ/፡፡ ለዚህም ነው ሐዋርያው “ዓለምን የፈጠረ እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም ሥጋ ለብሶ መጣ፤ ተገለጠ፤ ረቂቅ ሲሆን ገዝፎ ታየ፤ ዳሰስነውም” ያለን /1ዮሐ.1፡1-2፣ ቅ.አትናቴዎስ/፡፡ በእውነቱ ለዚህ አንክሮ ይገባል! እርሱ የማይደፈር ግሩም ነው፣ በእኛ ዘንድ ግን ትሑት ነው፡፡ እርሱ የማይመረመር ልዑል ነው፣ በእኛ ዘንድ ግን አርአያ ገብር ሥጋን ተዋሐደ፡፡ እርሱ የማይያዝ የማይዳሰስ እሳት ነው፣ እኛ ግን ያዝነው ዳሰስነውም /አባ ሕርያቆስ/፡፡
 ነገር ግን እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም ቢመጣም ሆን ብለው ዓይነ ልቡናቸውን ለጨፈኑ አላበራም፤ አያበራምም /ማቴ.13፡14-15/፡፡ እነዚህ ዓይነ ስዉራን (ልበ ስሑታን) የእግዚአብሔር ነገር ሲነገራቸውም እንደ ሞኝነት ይቆጥሩታል /1ቆሮ.2፡14፣ ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ/፡፡ እኛም ብንሆን ልቡናችን በኃጢአት ጨለማ ከተጋረደ ብርሃኑን ማየት አንችልም፤ ኃጢአትን ከእኛ ስናርቅ ግን ወደ እውነተኛው ብርሃን እየቀረብን እንሄዳለን /ማቴ.5፡8፣ ቅ.ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ/፡፡ ይህንን ብርሃን ለማየት ዓይነ ልቦናችን የተከፈተ ሲሆን በብርሃኑ እንመላለሳለን /ቅ.ቄርሎስ/፡፡ በእርግጥም በጽድቅ ጐዳና የሚሄድ ሰው መላ ዘመኑ የብርሃን ሕይወት ነው /ዓይነ ስወሩ ዲዲሞስ/፡፡
“በዓለም ነበረ፥ ዓለሙም በእርሱ ሆነ፥ ዓለሙም አላወቀውም። የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም። ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።” ዮሐ.1፡10-13
 እንዴት ያለ ድንቅ ቸርነት ነው?! አካላዊ ቃል በዓለም የነበረ ቢሆንም ከዓለም ጋር እኩል ዕድሜ አልነበረውም /መዝ.90፡2/፡፡ አመጣጡም እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ በዓለሙ የሌለ ሁኖ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ወንጌላዊው እንዲህ እንዳናስብ “ዓለሙም በእርሱ ተፈጠረ” ብሎ ይቀጥላልና፡፡ በዚሁ ቃል መሠረት ማንም ሰው ይመንም አይመንም የወልድ ቅድመ ዓለም መኖር አያስቀረውም፡፡ የቃልን እግዚአብሔርነት አያጐድለውም፡፡ በዚህ ዓለም ጥበብ የሚመላለስ ሰውስ ይህ ምሥጢር እንዴት ሊገባው ይችላል /1ቆሮ.2፡14/?! የሚገርመው ደግሞ ዓለም ያላወቀችው ወልድን ብቻ ሳይሆን አባቱንም ጭምር መሆኑን ነው /ዮሐ.17፡25፣ ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ/፡፡
 ሰው ወዳጅ የሆነው አምላካችን እኛ በፈቃዳችን የማይበላውን በልተን ብንቆሽሽም እንደ ቆሸሽን እንቀር ዘንድ አልወደደም፡፡ ስለዚህ እርሱ ራሱ በደሙ ካልወለወለን በስተቀር መልአክም ይሁን ሰው ሊያስታርቀን ስላልቻለ ፍቅሩ አስገድዶት የእኛን ባሕርይ ባሕርይ አድርጐ መጣ /ቅ.አትናቴዎስ/፡፡ ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ ወአብጽሖ እስከ ለሞት- የሰው ፍቅር ወልድን ከዙፋኑ ስቦ ጎትቶ አወረደው፤ እስከ ሞት ድረስም አደረሰው /አባ ሕርያቆስ/፡፡ አንድ ዐይነ ስውር ሰው ፀሐይን ባያይ ፀሐይዋ ስለሌለች ሳይሆን እርሱ ሊያያት ስላልቻለ ነው፡፡ ይህንን የክርስቶስ ፍቀር ያላወቁ ሰዎችም እንዲህ ናቸው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ፡- “የእግዚአብሔር ምሳሌ የሆነ የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን እንዳያበራላቸው፥ የዚህ ዓለም አምላክ (ዲያብሎስ) የማያምኑትን አሳብ አሳወረ” እንዲል /2ቆሮ.4፡4፣ ቅ.ቄርሎስ/። የሰው ልጅ በሙሉ ለእግዚአብሔር በእግዚአብሔር ቢፈጠርም የዚህ ዓለም ገዢ የተባለው ዲያብሎስ ግን እስራኤል ከእግዚአብሔር የተሰጣቸውን ሕግ በማስተው፣ አሕዛብን ደግሞ በአምኮተ ጣዖት በማሳወር ፈጣሪያቸውን እንዳያውቁት አደረገ /ኢሳ.1፡2-4/፡፡ መዝሙረኛው ይህ ነገር ቢያስደንቀው “አእምሮ የሌለው ክቡር ሰው እንደሚጠፉ እንስሶች መሰለ” አለ /መዝ.49፡20፣ ቅ.ቄርሎስ/፡፡
 ተወዳጆች ሆይ! እነሆ እግዚአብሔር እንዴት እንደወደደን ታስተውሉ ዘንድ እንማልዳችኋለን /1ዮሐ.3፡1/፡፡ ወልድ እኛን ወንድሞቹ ያደረገን ብቻውን ስለሆነ አልነበረም ፡፡ ወንድሞቹ ያደረገን ፍቅሩ ብቻ ነው፤ ወንድሞቹ ያደረገን የዘላለምን ሕይወት እንድንወርስ ስለወደደ ብቻ ነው፤ እርሱ ከእኛ ይጠቀም ዘንድ አላዳነንም /ዮሐ.3፡16/፡፡ እርሱ የመጣው ለተቀበልነው ሁሉ በጸጋው የእግዚአብሔር ልጆች እንሆን ዘንድ ሥልጣን ሊሰጠን ነው /ዮሐ.1፡12/፡፡ ታድያ እርሱ ሊያነሣን ወዶ ሳለ እኛ አንነሣም የምንለው ለምንድነው? ልጅነትን አንቀበልም ብለንስ ወድቀን እንቀር ዘንድ ለምን እንመርጣለን? /አውግስጢኖስ/፡፡ እርሱ “አማልክት ዘበጸጋ ናችሁ” ብሎ የልዑል ልጆች ሊያደርገን ፈልጐ ሰው ሲሆንልን እኛ እንደ ዲያብሎስ ለምን ወድቀን እንቀራለን? /መዝ.81፡6-7፣ ቴዎዶር ዘስይርጥ/፡፡ ስለዚህ ከተዋሕዶ ብርሃን ርቃችሁና ክርስቶስን ባለማወቅ ጨለማ ውስጥ ያላችሁ ሁሉ ዛሬ የእግዚአብሔር ልጆች ሆናችሁ ሥልጣንን እንድታገኙ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠመቁ /ማቴ.28፡19፣ ቅ.ባስልዮስ/፡፡ በክርስቶስ ስታምኑና መዳናችሁን ወደምትፈጽሙበት ልምምድ ስትገቡ ከወንድና ከሴት ፈቃድ ሳይሆን ከሥላሴ ፈቃድ ዳግመኛ ትወለዳላችሁ /ዮሐ.1፡13/፡፡ እግዚአብሔር ዛሬም ይወዳችኋል፤ ይጠራችኋልም፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑት አምላካችሁ በጠባብ ደረትና በአጭር ቁመት ከሴት የተወለደው እናንተ ከእርሱ ትወለዱ ዘንድ ነው፡፡ የሞተላችሁም እናንተ ሞት ይቀርላችሁ ዘንድ ነው /አውግስጢኖስ/፡፡
 የሥላሴን ልጅነት አግኝታችሁና ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ኪዳን ለተጋባችሁ ለእናንተም  ወንጌላዊው ሲናገር “የእግዚአብሔርን ልጅነት ሰጣቸው” ሳይሆን “የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው” እንዳለ አስተውሉ፡፡ ምክንያቱም በጥምቀት የተከፈተልንን መዳን የምንፈጽመውና እግዚአብሔርን ወደ መምሰል ሙላት የምንደርሰው ልጅነታችንን እስከ መጨረሻ ያለነቀፋ ስንይዝ ብቻ ነው /ማቴ.10፡22/፡፡ ምክንያቱም ልጅነታችንን ከእኛ ንዝህላልነት ካልሆነ በስተቀር ማንም መልሶ ሊወስዳት አይችልምና /ማቴ.25፡1-13፣ ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ/፡፡ አዎ! ይህን ስናደርግ ከእንግዲህ ወዲህ ወዳጆች ነን እንጂ ባሮች አይደለንም፤ ልጆችም ከሆንን ደግሞ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ወራሾች ነን /ሮሜ.8፡17፣ ገላ.4፡7፣ ቅ.ዮሐንስ ዘደማስቆ/፡፡
 ስለዚህ ሁላችንም የመዳናችን ቀንድ ወደ ሆነው ወደ ክርስቶስ እንመለስ፡፡ እርሱ በጨለማና በሞት ጥላ ሥር ተቀምጠን ለነበርን ለሁላችን ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀውን ያወርሰን ዘንድ የመጣ እውነተኛ ብርሃን ነው /ሉቃ.1፡79፣ 2ቆሮ.2፡9/፡፡ እንግዲያስ ሰው ብቻ መሆን ይብቃን፤ የእግዚአብሔር ልጆች ለመሆንም ልጅነትን እንቀበል፡፡ ከተቀበልን በኋላም ሁል ጊዜ እንደ መላእክት ክብሩን እናይ ዘንድ ልበ ንጹሐን እንሁን /ማቴ.5፡8፣ አውግስጢኖስ/፡፡
 መንግሥተ ሰማያትን ለመውረስ እኛ ሥራ ሠርተን አንበቃምና ሰውን በመውደድ ሰው የሆነው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነቱ ብዛት መንግሥቱን ያድለን፡፡ አሜን /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ/!!
  ሰላም ወሰናይ!

FeedBurner FeedCount