Wednesday, August 22, 2012

በአዲሲቷ ቆሮንቶስ መኖር(ለሕፃናት)!


  እንደምን አላችሁ ልጆች? ጾመ ፍልሰታ እንዴት አለፈ? ጾማችኋል አይደል? ጐበዞች!
ለዛሬ አንድ በጣም ጣፋጭ ታሪክ ይዤላችሁ ቀርቤአለሁ፡፡ ለመስማት ዝግጁ ናችሁ አይደል? ጐበዞች!
   ከዕለታት በአንዲቱ ቀን ማርቆስ ሁል ጊዜ ከሚያጠናባት ክፍል ተቀመጠና መጽሐፍ ቅዱስን አንሥቶ የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕራፍ 13 ላይ ስለ ፍቅር ማንበብ ጀመረ፡፡ ነገር ግን ደጋግሞ ቢያነበውም ፍቅር ምን ማለት እንደሆነና እንዴት ተግባራዊ እንደሚደረግ አልገባ አለው፡፡ እያሰላሰለ ሳለም በተቀመጠበት ወንበር እንቅልፍ ወሰደውና ደስ የሚል ሕልም አየ፡፡ ከነቃ በኋላም ያየውን ሕልም በወረቀት እንዲህ ብሎ ጻፈው፡-
“የሆነ አንድ ፌርማታ ላይ የአውቶብሳችንን መምጣት እየጠበቅኩ የነበርኩ ይመስለኛል፡፡ ከጎኔም አንድ ሰውዬ እንደኔ አውቶብስ ሲጠብቅ ቆሞ አየሁኝ፡፡ ሰውዬውም፡- እኔ ጋር ና አለኝ፡፡ እኔም ሄድኩና አንድ ላይ ተሳፈርን፡፡ ፊት ለፊትም እየተያየን ተቀመጥን፡፡ አውቶብሳችን መንቀሳቀስ ጀመረች፡፡ ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላም አውቶብሳችን የመጀመርያው ፌርማታ በምትሆን “አዲሲቷ ቆሮንቶስ” በምትባል ስፍራ ደረስን፡፡ ሁለታችንም ወረድን፡፡ አንድ ላይ በእግር እየተንሸራሸርን ሳለ (Walk እያረግን ሳለ) ሰውዬውን ቀና አልኩና ትኩር ብዬ ተመለከትኩት፡፡ እርሱም ፈገግ ብሎ አየኝ፡፡ በፊቱ የሆነ የሐሴትና የደስታ ነገር ይነበባል፡፡ እኔም በውስጤ ደስ የሚል ስሜት ተሰማኝ፡፡ በዚያ አከባቢ እንደኛ ሲንሸራሸሩ የማያቸው ሰዎች ሁሉም በእርጋታ ቀስ ብለው ይንቀሳቀሳሉ፡፡ ሳስተውላቸው አንድ ሰው ስንኳ ፊቱ የተቋጠረ የለም፡፡ እኛም ከትንሽ ደቂቃዎች በኋላ የፍቅር አደባባይ ወደተባለ አደባባይ ደረስን፡፡ በአደባባዩ መኻከል ላይ አንድ ትልቅ የውኃ ፏፏቴ (ፋውንቴን) ይታያል፡፡ አደባባዩ ዙርያው በትልልቅ ሥዕሎች (ቢል ቦርዶች) ተሞልቷል፡፡ ሰውዬም በጣቱ ወደ አንድ ሥዕል እየጠቆመ፡- “እዛ ጋር ያለው ትልቁን መስቀል አየኸው? ይህ ሥዕል የክርስቶስን ነገረ ስቅለት የሚያሳይ ሥዕል ነው” አለኝ፡፡ እኔም ክርስቶስ የተሰቀለበትን ሥዕል ለማየት ቀና ስል ወዲያው እንዲህ የሚል ጽሑፍ ከስሩ አነበብኩኝ፡- “ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም” /ዮሐ.15፡13/፡፡ ከአጠገቡ ወደ ነበረው ሌላ ሥዕል ስመለከት ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ በጉልበቱ ተንበርክኮ ሲጸልይ አየሁት፡፡ ሲጸልይ የተናገራቸው ቃላትም ከሥዕሉ ግርጌ እንዲህ ተጽፈዋል፡- “ጌታ ሆይ ይህን ኃጢአት አትቁጠርባቸው” /ሐዋ.7፡60/፡፡ ዐይኔን ወደ ሌላኛው ማዕዘን ሳሻግረው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልጇ ወዳጇን ታቅፋ አየኋት፡፡ እመቤታችን ያቀረበችው የምስጋና መዝሙርም እንዲህ ተብሎ ተጽፏል፡- “ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፡፡ መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደረጋለች፡፡ የባርያይቱን ውርደት ተመልክቷልና፡፡… ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራን አድርጓልና ስሙም ቅዱስ ነው” /ሉቃ.1፡46-49/፡፡ ወደ ሌላኘው ማዕዘን ዐይኔን ሳማትር የጠፋው ልጁን ለመቀበል ሐሴት የሚያደርገውን አባት ተመለከትኩት፡፡ በዚያም እንዲህ የሚል ጽሑፍ ነበረ፡- “እንብላ ደስም ይበለን፤ ይህ ልጄ ሞቶ ነበርና ደግሞም ሕያው ሆኗል፤ ጠፍቶም ነበር ተገኝቷልም” /ሉቃ.15፡23-24/፡፡
  ከዚያ በኋላ የሆነ መቀመጫ አገኘንና አንድ ላይ ተቀመጥን፡፡ ሰውዬውን “አደባባዩን በጣም ወደድኩት” አልኩት፡፡ ሰውየውም ሐሳቤን በአወንታ ተቀብሎ ራሱን ነቀነቀና እንዲህ አለኝ፡- “አየህ ልጄ! በዚህ አደባባይ ቂም በቀል የሚባል ነገር አይታወቅም፡፡ አንዱ በአንዱ አይቀናም፡፡ ሰላም ሲባባሉ ራሳቸውን ጐንበስ አድርገው በትሕትና ነው፡፡ ፍቅራቸው በጣም ልዩ ነው፡፡ ጌታ እንዳስተማረው እዚህ የምታየው ሰው ሁሉ ባደረገው ነገር “እኔ እኮ እንዲህ አደረግኩ” ብሎ አይመካም፡፡ ሁሉም ተራ በተራ ይደማመጣሉ እንጂ አንድ ሰው ስንኳ ድምጹን ከፍ አድርጎ አይናገርም፡፡ አንድ ስንኳ ተቈጥቶ የሚናገር የለም፡፡ እንደ አንተ ዓይነት ሕፃን በዚህ ቦታ ወይም በመማርያ ክፍል ከጓደኞቹ ጋር ከተቀመጠና እየተናገረ ከሆነ ሁሉም በጽሞና ያደምጡታል፡፡ እርሱም ሌሎች ሕፃናት ሲናገሩ በጽሞና ያደምጣቸዋል፡፡ ከጓደኛቸው አንዱ ምናልባት የተለየ ሐሳብ እንኳን ቢኖረው ያሳምናቸዋል እንጂ የእኔ ብቻ ነው ትክክል አይላቸውም፡፡ አሁንም ሌላ ሕፃን ምናልባት… ምናልባት ተሳስቶ ልክ ያልሆነ ነገር ቢናገር ቀስ አድርገው ልክ የሆነውን ይነግሩታል እንጂ ማንም ስለተሳሳተ አይስቅበትም፡፡ በቃ! እንዲህ እያደረጉ እከሌስ ጥሩ ልጅ አይደለም ተብሎ ሰው ሲያወራለት የነበረው ልጅ በአንዴ ይለውጡታል፡፡ እርሱም ጐበዝ ልጅ ይሆናል፡፡ ተራ በተራ ሁሉም ከተናገሩ በኋላ በአንድ ሐሳብ ተስማምተው ይጨርሳሉ፡፡ ሲጨርሱም ሁሉም ተቃቅፈው እየተጫወቱ ይሄዳሉ፡፡ ሲጫወቱ ደግሞ ሐቅ ሐቁን ብቻ ይነጋገራሉ እንጂ አይወሻሹም፡፡ የሚደባበቁት ምንም ነገር የላቸውም፡፡ አንዱ በሚናገረው ነገርም ሌላው ያምኗል፡፡ እናም በቃ ሁሉም ነገር የሚያደርጉት በፍጹም ፍቅር ነው፡፡ ወደየቤታቸው ሲገቡም ተጨባብጠው ደኅና እደሩ ተባብለው ይለያያሉ፡፡”
 ከዚህ በኋላ ሰውዬውን፡-“ወይኔ! ሁል ጊዜ እዚህ በሆንኩኝ? ከእነዚህ ልጆች ጋር መጫወት እፈልጋለሁ?” አልኩት፡፡ ሰውዬውም ልብ ውስጥ በሚዘልቅ ፈገግታ ራሴን እየዳበሰ እንዲህ አለኝ፡- “ይህን በሕይወትህ ማድረግ እኮ በጣም ቀላል ነው፡፡ ሁሉም ነገር የምትወስነው አንተ ነህ፡፡ ልብህ በእነዚህ ልጆች እንዳየኸው አድርገህ ሁሉም ሰው እኵል የምታፈቅር ከሆነ በጣም ቀላል ነው፡፡ እንዲህ የምታደርግ ከሆነ እዚህ ያየሃቸው ሁሉም በአንተ ሕይወት ይከናወናሉ፡፡ እንዲህ ስታደርግ ሁሉም ነገር በፍቅር ማየት ትጀምራለህ፡፡ ሊደርሱብህ የሚችሉ ችግሮች እንኳን በጣም ጠቃቅንና በቀላሉ የምትፈታቸው ይሆናሉ” አለኝ፡፡ እኔም ንግግሩን አቋረጥኩትና፡- “የሆነ የሰፈራችን ልጅ ዝም ብሎ የሚሰድበኝ ከሆነ ምንም ነገር ሳልመልስለት እንዴት እችላለሁ? እንዲህ ዓይነቱን ልጅስ እንዴት ልወደው እችላለሁ?” ብዬ ጠየቅኩት፡፡ ሰውዬውም እንዲህ ሲል መለሰልኝ፡- “አየህ! ፍቅር ከሁሉም ይበልጣል የተባለው ለዚህ ነው፡፡ አንተ በአዲሲቷ ቆሮንቶስ ከእነዚህ ልጆች ጋር መኖር ከፈለግክ ሁል ጊዜ ፍቅርን በተግባር በመግለጥ መለማመድ አለብህ፡፡ አንተ በምትኖርባት መንደር ሆነህ በልብህና በሐሳብህ እዚች ከተማ መኖር ትችላለህ፡፡ ፍቅር ከስጦታዎች ሁሉ እንደምትበልጥና የመልካም ምግባር ሁሉ እናት እንደሆነች ታውቃለህ?” ሲለኝ ከእንቅልፌ ብንን ብዬ ነቃሁ፡፡ ዓይኔን አሻሽቼ ዙርያዬን ስመለከት ሰው የለም፡፡ ባየሁት ሕልም ግን በጣም ተደሰትኩኝ፡፡ መጽሐፍ ቅዱሴንም ሳዬው 1ኛ ቆሮንቶስ ምዕራፍ 13 ላይ እንደተገለጠ ነበር፡፡ 

 ልጆች! ታሪኩን ወደዳችሁት አይደል? ጐበዞች! “እኛም እንደ አዲሰቱ ቆሮንቶስ ልጆች እንሆናለን” እንደምትሉ እርግጠኛ ነኝ፡፡ በሉ ሌላ ጊዜ ሌላ ታሪክ ይዤላችሁ እስክመጣ ድረስ ደኅና ሰንብቱ! እወዳችኋለሁ እሺ?!
(ምንጭ፡-The Coptic Orthodox Diocese of the Southern USA, Sunday school Curriculum, Grade 8)
   

Thursday, August 16, 2012

የቅዱሳን ሕይወት- ክፍል ሁለት!


    በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
 በቅዱሳን  ሕይወት ውስጥ የምንመለከተው እኛን ለማዳን ሲል ሰው የሆነውን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ነው። የተቀደሰና ዘላለማዊ ሕይወትን ማግኘት የሚቻለው በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋ መልበስ፣ ሞትና ትንሣኤ ነውና። እርሱ የኛን ባሕርይ ባሕርይ አድርጎ ሞት ውላጤ የሚስማማው የነበረ ባሕርያችንን የማይሞት የማይጠፋ አደረገው። በገዛ ጥፋታችን ያመጣነውን የማይገፋ የነበረ ጠላታችን ሞትን በሥጋ ቀምሶ በልዩ ትንሣኤው አሸነፈልን። መድኃኒት የሆነ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን በኃጢአት በቆሰለ ሰውነታችን ላይ በመጨመር ከኃጢአታችን እንድንፈወስ፣ ከእርሱ ጋር አንድ እንድንሆን አደረገ። ይህን ሁሉ የማዳን ሥራ ከፈጸመ በኋላ ከዚህ በኋላ እኛ ደግሞ እርሱን እንድንመስል ምሳሌ ትቶልን እርሱ በሚሰጠን ይልና ጸጋ ሞትን (ሐጢአትን፣ ዓለምን) እንድናሸንፍ አዝዞን በክብር ወደ ሰማይ ረገ።ለዚህ ተጠርታችኋልና፤ ክርስቶስም እኮ ፍለጋውን ትከተሉ ዘንድ ምሳሌውን ሊተውላችሁ ስለእናንተ መከራን ተቀብሏል።” (፪ጴጥ.*፳፩)ከእኔም ተማሩ፤ እኔ የዋህ ነኝና፤ ልቤም ትሑት ነውናእንዲል (ማቴ.፲፩*፳፱)

 ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በዐይናቸው ዐይተው በጆሯቸው ሰምተው ይህን ያዩትንና የሰሙትን ለዓለም መሰከሩ።የእናንተ ግን ዐይኖቻችሁ ያያሉና፣ ጆሯችሁም ይሰማሉና ብፁዓት ናቸው። እውነት እውነት እላችኋለሁ ብዙዎች ነብያትና ጻድቃን እናንተ የምታዩትን ሊያዩ ተመኝተው አላዩም፣ እናንተ የምትሰሙትንም ሊሰሙ ተመኝተው አልሰሙምእንዲል (ማቴ.፲፫*፲፮ -፲፯ ) በብሉይ ኪዳን የነበሩ ነብያትና ቅዱሳን የክርስቶስን መምጣት ከሩቅ ሆነው በትንቢታቸው በእምነት ተመለከቱ እንጂ በዐይነ ሥጋ አላዩም፤ ዐረፍተ ዘመን ገትቶአቸዋልና። ቅዱሳን ሐዋርያት በእርሱ ቸርነት ለዚህ ክብር ተመረጡ። ይህንንም ያዩትንና የሰሙትን ለዓለም ሕዝብ በብቃት መሰከሩ፤ አስተላለፉ። ቅዱሳን ሐዋርያት ምስክርነታቸው በቃል በማስተማርና በተግባር ደግሞ በሥራ በማሳየት ነበር። ስለሆነም እንደዚህ ብለውደፍረውእስከመናገር ደረሱ፡-እኔ ክርስቶስን እንደምመስለው እኔን ምሰሉ” (፩ቆሮ.፲፩*) ቅዱሳን ደግሞ ይህንን የሐዋርያትን ሕይወት በመከተል ሐዋርያትን መስለውና አህለው ተነሥተዋል፤ ገናም እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ ይነሣሉ።

 ታዲያ የእነዚህን ቅዱሳን ሕይወት ማንበብና ማወቅ ለእኛ መንፈሳዊ ሕይወት ምን ዐይነት ፋይዳ አለውበቅዱሳን ሕይወትስ እንዴት መጠቀም እንችላለንከላይ እንደተመለከትነው የቅዱሳን ሕይወት ክርስቶስን የመልበስና በሁለንተናዊ ኑሮአቸው እርሱን የመምሰል ሕይወት ነው። ታዲያ እኛስ የምንፈልገው ይህንኑም አይደልበዚህ ረገድ ቅዱሳን በመከራ ተፈትነው ፈተናውን በሚገባ ያለፉና በድል ያሸነፉ በመሆናቸው በሕይወት ማደግ ለምንፈልግ ለኛ የተግባር ምህርት ቤቶች ናቸው። እነርሱ ፍጹማን ክርስቲያኖች ስለሆኑና ክርስቶስን ስለሚመስሉ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ (ወንጌልን) በመፈጸም መንፈሳዊ ፍሬ ያፈሩና እውነተኛ የወንጌል ገበሬዎቸ ናቸው። እነርሱ ወንጌልን በተግባር ኑረው ባያሳዩን ኖሮ በሰው የማትቻል ምናባዊ (ideal) ሕግ ሆና ትቀር ነበር። ስለዚህ ሕይወተ ቅዱሳን የወንጌል ተግባረ ዕድ (‘applied or practical’ ወንጌል) /ቤት ነው። ይህንንም የተለያዩ የቅዱሳን ገድላትን፣ ድርሳናትንና እንዲሁም ስንክሳርን ስናነብ የምንገነዘበው ነው። ይህንን ሐሳብ የሚያጠናክር አንድ አባት ሲያስተምሩ የሰማሁትን ላካፍላችሁ።
  • በሚሰድቧችሁና በሚያሳድዷችሁ ጊዜ፣ ስለእኔም እየዋሹ ክፉውን ሁሉ በሚናገሩባችሁ ጊዜ ብፁዓን ናችሁ። ደስ ይበላችሁ ሐሴትንም አድርጉ…” (ማቴ*፻፩-፻፪) ለዝርዝሩየሐዋርያት ሥራ :- “ሐዋርያትንም ጠርተው ገረፉአቸው እንግዲህ ወዲህም በኢየሱስ ስም እንዳያስተምሩ ገሥጸው ተዉአቸው። እነርሱም ከሸንጎው ፊት ደስ እያላቸው ወጡ”(*-፵፩)
  • ጠላቶቻችሁን ውደዱ፤ ለሚጠሏችሁም መልካም አድርጉ። የሚረግሟችሁንም መርቁአቸው፤ ለሚበድሏችሁም ጸልዩላቸው” (ሉቃ*፳፯-፳፰) ለዝርዝሩ የሐዋርያት ሥራ :-“ከከተማም ወደ ውጭ ጎትተው አውጥተው ወገሩት … በጉልበቱም ተንበርክኮ አቤቱ ይህን ኃጢኣት አትቁጠርባቸው ብሎ ጮኸ።” (ሐዋ.*)
  • አምላክህ እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም ይልህ ውደደው” (ማቴ፳፪*፴፯) ለዝርዝሩ ወደ ሮሜ ሰዎች :- “ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ ነውንኀዘን ነውንስደት ነውንራብ ነውንመራቆት ነውንጭንቀት ነውንሾተል ነውን? ... ከክርስቶስ ፍቅር ሊለየን የሚችል የለም (ሮሜ. *፴፭)
  • እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን እኔ የምሠራውን ሥራ እርሱም ይሠራል፤ ከዚያም የሚበልጥ ይሠራል።” (ዮሐ፲፬*፲፪) ለዝርዝሩ ገድለ ጊዮርጊስ፡፡
  • ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢገዛ ነፍሱንም ቢያጣ ለሰው ምን ይረባዋል?” (ማቴ፲፮*፳፯) ለዝርዝሩ የአባ ጳውሊ ታሪክን ይመልከቱ፡፡
  • . . .
 እኛም  እንደእነርሱ ተግባራዊ የወንጌል ሕይወትን ለመኖር ከሕይወታችው ለመጠቀም የሚከተሉትን ነጥቦች ተግባራዊ እናድርግ :-
. ቅዱሳንን  የሕይወታችን ምሳሌ ማድረግ :- ቅዱሳን በሙሉ በሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ቃል እንዲህ ይሉናል፡-እኔ ክርስቶስን እንደምመስለው እኔን ምሰሉ” (፩ቆሮ.፲፩*) እውነተኛና ተግባራዊ ሕይወትን እንዴት መኖር እንዳለብን ከሕይወታቸው መማርና ዘወትር እነርሱን ለመምሰል መታገል አለብን።
. ቅዱሳንን የቅርብ ወዳጆቻችን ማድረግና በጸሎታችን እርዳታቸውን መጠየቅ :- እኛ የምናምነው እምነት ቅዱሳን ያመኑትን ነው፤ ልንደርስበት የምንፈልገውም የቅድስና ሕይወት እነርሱ የኖሩትን ነው። ስለዚህ ቅዱሳን በእምነት ወንድሞቻችን እህቶቻችን ስለሆኑና ምንም እንኳ በሥጋ ቢለዩም በነፍስ ሕያዋን ስለሆኑ ብንጠራቸው ይሰሙናል፣ ይረዱናል። በቦታና በጊዜ ከማይወሰነው ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ስለሆኑ እነርሱም የጸጋ ምልአት (ያለመወሰን) ተሰጥቷቸዋል። ስለሆነም በየትኛውም ጊዜና ቦታ ሆነን ብንጠራቸው በረድኤታቸው ያግዙናል።
. ዜና ገድላቸውን ዘወትር ማንበብ:- ቅዱሳን ስለ ክርስቶስ ፍቅር ሰይጣንንና ዓለምን ከነኮተቱ አሸንፈው እንዴት ለክብር እንደበቁ ለማወቅና ከእነርሱ ልምድ ለመቅሰም ሁሌም ታሪካቸውን ገድላቸውን ማንበብ አለብን።
. ቅዱሳን ልክ እንደኛ ሰዎች እንደሆኑ ማሰብ:- ቅዱሳን ስለ ክርስቶስ ፍቅር ሕይወታቸውን የሠዉት፣ ዓለም በቃኝ ብለው በየበረሃው የዞሩት የተለዩ ፍጡሮች ስለሆኑ አይደለም። እነርሱም እንደኛው ሥጋን የለበሱ ፍጡራን ናቸው። እኛን የሚያምረን የሚያምራቸው፣ ለኛ የሚያጋ*ጥሙን መከራዎች በሙሉ ያጋጠሙአቸው (እንዲያውም በበለጠ) ናቸው። ነገር ግን በእምነታቸውና ለክርስቶስ ባላቸው ፅኑ ፍቅር ሁሉን ተፈትነው በመጨረሻ በድል አድራጊነት የቋጩ ስለሆነ ዘወትር ሕያው ምስክር ይሆኑናል።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
ይቀጥላል!


ክፍል አንድን ለማበብ ይህን ይጫኑ
http://mekrez.blogspot.com/2012/08/blog-post.html

FeedBurner FeedCount