Monday, November 3, 2014

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል አምስት)


(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 25 ቀን፣ 2007 ..)- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


ሐ) ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ አረዳድ


 እንደምን ሰንበታችኁ ውድ የመቅረዝ ተከታታዮች? ትምህርተ ሃይማኖት በሚለው ተከታታይ ትምህርታችን ውስጥ ለዛሬ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ኦርቶዶክሳዊ አረዳድን እንማማራለን፡፡ በዚኽ ጽሑፍ ውስጥ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ምንነት፤ በቤተ ክርስቲያን ያለው ቦታ ምን እንደሚመስልና እንዴት መረዳት እንዳለብን እና ሌሎች ተያያዥ ሐሳቦችን እንመለከታለን፡፡ መልካም ንባብ፡፡

Wednesday, October 29, 2014

ስለ አቤልና ቃየን (ለሕፃናት)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 20፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የተዋሕዶ ፍሬዎች፣ የሃገር ተስፋዎች እንደምን ሰነበታችኁ ልጆች? “እግዚአብሔር ይመስገን ደኅና ነን” አላችችኁ? መልካም፡፡ ትምህርት እንዴት ነው? እየጐበዛችኁ ነው አይደል? ጠንከር ብላችኁ በማጥናት ከአምናው የተሻለ ውጤት ለማምጣት እንደተዘጋጃችኁ ተስፋ አደርጋለኹ፤ በርቱ እሺ?
  ዛሬ አቤል እና ቃየን ስለሚባሉ ኹለት ወንድማማቾች ታሪክ ነው ይዤላችኁ የመጣኹት፡፡ ለመስማት ዝግጁ ናችኁ አይደል? በጣም ጥሩ!!!
 አዳምና ሔዋን በገነት ይኖሩ ነበር፡፡ ሲበድሉ ግን እግዚአብሔር ከገነት አስወጣቸው፡፡ ደብር ቅዱስ ወደ ተባለ ቦታም ተሰደዱ፡፡ ከዚኽ ቦታ ኾነውም የገነት ሽታ እየሸተታቸው ይኖሩ ነበር፡፡ ወደ ገነት ግን መቅረብ አልተቻላቸውም፡፡ ሦስት ዓመት ሙሉም በጣም ያለቅሱና ያዝኑ ነበር፡፡

Monday, October 27, 2014

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (መንደርደሪያ)



በዲ/ን ሳምሶን ወርቁ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 17 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
በክርስትና ሕይወት ውስጥ ምዕመናን ስለመንፈሳዊነት ያላቸው ግንዛቤ ብዙ ጊዜ ያልተሟላ አንዳንዴ የተሳሳተ ብቻ ሳይሆን መንፈሳዊነት ብለው የሚያስቡት መንፈሳዊነት ያልሆነውን ሆኖ ይገኛል፡፡ ከዚህ የተነሣ ብዙዎች መንፈሳዊያን ናቸው ብለው የሚያስቧቸውን ሰዎች ሕይወት ተመልክተው መንፈሳዊነት እንዲህ ከሆነ ይቅርብኝ እስከማለት ይደርሳሉ፡፡ ነገር ግን መንፈሳዊነት ትርጉሙ ዓላማው ምስጢሩ የረቀቀ የጠለቀ ነው፡፡

Saturday, October 25, 2014

እኔ ነኝ፥ አትፍሩ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 15 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ከዕለታት በአንዲቱ ቀን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር በተመላለሰ ጊዜ ወደ ምኵራብ ገባ፡፡ እንደ ባለ ሥልጣንም ያስተምራቸው ነበር፡፡ ብዙዎች ግን ሰምተው ተገረሙና፡- “እነዚህን ነገሮች ይህ ከወዴት አገኛቸው? ለዚህ የተሰጠችው ጥበብ ምንድር ናት? በእጁም የሚደረጉ እንደነዚህ ያሉ ተአምራት ምንድር ናቸው? ይህስ ጸራቢው የማርያም ልጅ የያቆብም የዮሳም የይሁዳም የስምዖንም ወንድም አይደለምን? እኅቶቹስ በዚህ በእኛ ዘንድ አይደሉምን?” እያሉ ይሰናከሉበት ነበር /ማር.6፡3/

FeedBurner FeedCount