Showing posts with label አቡነ ተክለሃይማኖት ገድል. Show all posts
Showing posts with label አቡነ ተክለሃይማኖት ገድል. Show all posts

Saturday, May 5, 2012

በአቡነ ተክለሃይማኖት ገድል ላይ የሚነሱ አንዳንድ ጥያቄዎች- (ለፕሮቴስታንቶችና ተሐድሶዎች የቀረበ)- ክፍል አንድ!=+=

አባታችን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በሰማዕትነት ሞተው ቅዱስ ጳውሎስ “እርሱንና የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ በመከራውም እንድካፈል ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢሆንልኝ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ” ያለውን ለመፈጸም ይመኙ ነበር /ፊሊ.3፡11/፡፡ ነገር ግን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደዌ ዘእሴት (ዋጋን በሚያሰጥ የሆድ ሕመም) እንዲሞቱ ነው የፈቀደላቸው፡፡ በዚህ አሟሟታቸውም ከጌታችን መከራ መስቀል እንደሚያሳትፋቸው እንደ ሰማዕትነትም እንደሚቆጠርላቸው ነው የተነገራቸው፡፡ ይህ ደግሞ ፍጹም መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት እንጂ መጽሐፍ ቅዱስን የሚቃረን አይደለም፡፡ ኢዮብን ስንመለከተው በደዌ ተልቶ ሸቶ ነበር፡፡ እንዲህ መሆኑ ግን ለጥቅሙ ነበር፡፡ ጳውሎስን ስናይ የጐድን ውጋት ነበረው /2ቆሮ.12፡7-10/፡፡ ነገር ግን ለጥቅሙ የተሰጠው ነበረ፡፡ ጢሞቲዎስን ስንመለከት የሆድ ሕመም ነበረው /1ጢሞ.3፡25/፡፡ ነገር ግን ለጥቅሙ ነበረ፡፡ ታድያ አቡነ ተክለሃይማኖት ዐስበ ሰማዕትነት (የሰማዕታትን ዋጋ) የሚያገኙበት ሕመም ያዛቸው ቢባል ምንድነው ብርቁ? አቡነ ተክለ ሃይማኖትም በዐረፍተ ዘመናቸው መጨረሻ የያዛቸው ደዌ ዘዕሴት ነበረ ቢባል ምንድነው ድንቁ? የክርስቶስን መከራ የሚያሳትፍ እንጂ የክርስቶስን መከራ የሚተካ አልተባለም፡፡ እንግዲያውስ ወንድሞችና እኅቶች! ያልተባለውን ተባለ፣ ያልተፈጠረውን ተፈጠረ፣ ያልተጣፈውን ተጣፈ እያልን ውሸት ከመናገር ብንቆጠብስ?(ይቀጥላል!)

 ተመሳሳይ ገጾች

 አባታችን ተክለሃይማኖት ማለት እኒህ ናቸው

FeedBurner FeedCount