Showing posts with label የሃይማኖታችን ሊቀ ካህናት- ክፍል አንድ. Show all posts
Showing posts with label የሃይማኖታችን ሊቀ ካህናት- ክፍል አንድ. Show all posts

Tuesday, June 19, 2012

የሃይማኖታችን ሊቀ ካህናት- ክፍል አንድ!!


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!   
    ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ስለ ሊቀ ካህናችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በስፋትና በጥልቀት የምናገኘው በዕብራውያን መልእክት ነው፡፡ ሐዋርያው መልእክቱን የጻፈበት ዓላማም በአጭሩ እንዲህ ቀርቧል፡- በይሁዳ ሀገርና በብሔረ አሕዛብ ሁሉ ያሉ ዕብራውያን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስንና ደቀ መዛሙርቱን ወንጌልን በማስተማራቸው አጽንተው ይጠልዋቸው ነበር፡፡ ጌታ ካረገ በኋላ ግን በሐዋርያት ቃል የሚደረገውን ተአምራት ባዩ ጊዜ ከእነርሱ ብዙዎች በጌታችን ስም አመኑ /ሐዋ.2 ሙሉውን ይመልከቱ/፡፡ ሆኖም ግን ሕገ ኦሪትን ከሕገ ወንጌል ይልቅ አብልጠው መጠበቃቸው አልተዉም፡፡ በሌላ አገላለጽ ሕገ ወንጌልን ለሕገ ኦሪታቸው ተጨማሪ ሕግ አድርገዋት ነበር፡፡

  ሐዋርያትም ሃይማኖተ ወንጌል በዓለሙ ሁሉ እስኪስፋፋ ድረስ ኦሪትን ከወንጌል ጋር እንዲጠብቁ ተዋቸው እንጂ “ኦሪታችሁን ፈጥናችሁ ልቀቁ” አላልዋቸውም ነበር፡፡ ከዚህም የተነሣ አይሁድ አሕዛብን ለጓደኝነት ይጸየፍዋቸው ምግባቸውም ከመብላት ይከለከሉ ነበር፡፡  ሐዋርያት ወንጌልን ሲያስተምርዋቸው ተአምራት ሲያደርጉላቸው አይተው ቢያምኑም ተገዘሩ፤ ሕገ ኦሪትን ጠብቁ ስላላልዋቸው ፍጹም ቅናት አደረባቸው፡፡ የኦሪታቸውና የሌዋውያን ክህነት የላሙን፣ የበሬዉን፣ የበጉን፣ የፍየሉን መሥዋዕትና በጠቅላላው የአባቶቻቸውን ሥርዓት ማለፍ ባሰቡ ጊዜ እጅግ አዘኑ፡፡ ከጥንት ጀምሮ ለእነርሱ ብቻ ይነገር የነበረው ተስፋ ለሁሉም እንደሆነ ባሰቡ ጊዜ እጅግ ታወኩ፡፡ ከዚህ በኋላ በአንድነት መከሩና ከአሕዛብ ወገን በወንጌል ያመኑትን “ወንጌል ያለ ኦሪት ጥምቀት ያለ ግዝረት አትረባምና ተገዘሩ ሕገ ኦሪትንም ጠብቁ” እያሉ ዓለምን የሚያውኩ ሐሰተኛ ወንድሞችን ወደ አንጾክያ ሰደዱ፡፡ የግብረ ሐዋርያት ጸሐፊ “ከይሁዳ ሀገርም የወረዱ ሰዎች እንደ ሙሴ ሕግ ካልተገዘራችሁ ልትድኑ አትችሉም እያሉ ወንድሞችን ያስተምሩ ነበር” እንዲል፡፡

  ስለዚህም በአንጾክያ ያሉ አሕዛብ እጅግ ታውከው ጳውሎስንና በርናባስን ተከራከሯቸው፡፡ ስለዚህ ክርክር ጳውሎና በርናባስ ከእነርሱም አንዳንዶች ሌሎች ሰዎች ወደ ሐዋርያት ወደ ቀሳውስትም ወደ ኢየሩሳሌም ይወጡ ዘንድ ተቈረጠ።

  ወደ ኢየሩሳሌምም በደረሱ ጊዜ ቤተ ክርስቲያንና ሐዋርያት ቀሳውስትም ተቀበሉአቸው፤ እግዚአብሔርም በአሕዛብ ዘንድ ተአምራት እንዳደረገላቸው አሕዛብም ሳይገዘሩ መንፈስ ቅዱስ እንደ ወረደላቸው ቢነግሯቸው ሐዋርያትና ቀሳውስቱ እጅግ ደስ አላቸው፡፡

  ከፈሪሳውያን ወገን አምነው የነበሩ አንዳንድ ሰዎች ግን ተነሥተው ወደ ሐዋርያት ሔዱና “ከአሕዛብ ያመኑትን ትገርዙአቸው ዘንድና ሕገ ኦሪትንም እንዲጠብቁ ታዙአቸው ዘንድ ይገባል” አሏቸው፡፡ ሐዋርያትና ቀሳውስት ግን በክርስትናው ታሪክ የመጀመርያው በሆነው በዚሁ ጉባኤያቸው “ከጣዖት ወደ ወንጌል በተመለሱ አሕዛብ ሸክም አታክብዱ፤ ሁላችንም በጸጋ እግዚአብሔር በወንጌል አንድ እንሆናለን እንጂ አባቶቻችን እኛም ያልቻልነውን ጽኑ ሸክም አታሸክሟቸው፡፡ ለጣዖት የተሠዋውን፣ ሞቶ ያደረውን፣ በደም የታነቀውን ከመብላትና ከዝሙት

FeedBurner FeedCount