Showing posts with label የምንጽፍበት ሰሌዳ. Show all posts
Showing posts with label የምንጽፍበት ሰሌዳ. Show all posts

Saturday, November 3, 2012

የምንጽፍበት ሰሌዳ!


 በዲ/ን ዳንኤል ክብረት



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
 ሁለት ጓደኞች ሞቃታማ በሆነው በረሃ እየሄዱ ነው። ብዙ ነገር እያነሡ ይወያያሉ። ታድያ የሆነ ጊዜ ወደ ክርክር ይገባሉ። አንዱ "እንዲህ ነው!" ሲል ሌላኛው "አይደለም" ይላል። "ነው" "አይደለም" "ነው" "አይደለም" እየተባባሉ ሲከራከሩ ፈርጠም ያለው ሌላኛውን በጥፊ አጮለው። በጥፊ የተመታው ደነገጠ። ቆይቶ ራሱን አረጋጋና ምንም ሳይናገር ቁጭ አለ። አጎንብሶም አሸዋው ላይ በጣቱ "ዛሬ በጣም የምወደው ጓደኛዬ በጥፊ መታኝ።" ብሎ ጻፈ። መቺው ቆሞ ያያል። ጓደኛውን በመምታቱና የተመታው ጓደኛውም ምንም ቃል አለመተንፈሱ ልቡን ነካው። ነገር ግን ይቅርታ እንኳ አላለውም።

FeedBurner FeedCount