Showing posts with label የዮሐንስ ወንጌል የ20ኛ ሳምንት ጥናት. Show all posts
Showing posts with label የዮሐንስ ወንጌል የ20ኛ ሳምንት ጥናት. Show all posts

Monday, May 21, 2012

የምናገርሽ እኔ እርሱ ነኝ- የዮሐንስ ወንጌል የ20ኛ ሳምንት ጥናት (ዮሐ.4፡16-26)!!


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ሳምራይቱ ሴት ያንን የሕይወት ውኃ፣ ያንን ዳግመኛ የማያስጠማ ምንጭ፣ ያ በደስታ የሚቀዱት መለኰታዊ ማየ ሕይወት ለመጠጣት ጎምጅታለች፡፡ ከወራጁ ውኃ ይልቅ ዕለት ዕለት ከሚፈልቀው ማየ ገነት፣ ከጸጋ መንፈስ ቅዱስ ትጠጣ ዘንድ ቸኩላለች፡፡ ስለዚህም፡- “ከዚህ አንተ ከምትለኝ ውኃ እንዳልጠማ ስጠኝ፤ ከእንግዲህ ወዲህ አባቴ ያዕቆብ ካስረከበኝ ጕድጓድ ይልቅ አንተ ከምትሰጠኝ ምንጭ እጠጣ ዘንድ እሻለሁ” ትሏለች፡፡ እንዴት ያለች ጥበበኛ ሴት ነች? እንዴት ያለች የምትደንቅ ሴት ነች? እንዴት ያለች እውነትን የተጠማች ነፍስ ነች? የጥበብ ባለቤት የሆነው ጌታችንም ሴትዮዋ ይበልጥ ኃጢአቷን እንድትናዘዝ፤ እንደ አለላ የሆነው ማንነቷ እንደ አመዳይ ነጽቶላት የሰላሙን ንጉሥም በልቧ ትሾመው ዘንድ በጥበብ ፡-“ሂጂና ባልሽን ጠርተሽ ወደዚህ ነዪ” ይላታል/ቁ.16፣ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ Homily.32/።
 
 ስለዚህም ሴቲቱባል የለኝም” ስትል ያለሐፍረት ትናገራለች፡፡ ጌታችንም ወደሚፈልገው አቅጣጫ ስለመጣችለት የሕይወቷን ምሥጢር፡- “ባል የለኝም በማለትሽ ውሸት አልተናገርሽም፤ ከዚህ በፊት አምስት ባሎች ነበሩሽና፡፡  አሁን ከአንቺ ጋር ያለው እንኳን ባልሽ አይደለም፤ በዚህስ እውነት ተናገርሽ” በማለት ይነግራታል /ቁ.18፣ አባ ሄሮኒመስ, Letter 108፡13/፡፡ እንዲህ ማለቱ ነበር፡- “ልጄ! እንዲህ በማለትሽ እውነት ተናግረሻል፡፡ ምክንያቱም አንቺ የምትመኪባቸው አምስቱ የሙሴ መጻሕፍት ድኅነተ ነፍስን ሊሰጡሽ አልቻሉምና፤ ጽምዓ ነፍስሽን ሊያረኩልሽ አልቻሉምና፡፡ እነርሱ ብቻ ሳይሆኑ በዚህ በሰማርያ የምታመልኪው ስድስተኛው ጣዖትም ሊያድንሽ አልቻለም፡፡ ስለዚህ እነዚህን ሁሉ ትተሸ፣ ከእነዚህ ሁሉ ጋር ተፋተሽ ከነፍስሽ እጮኛ ከእኔ ጋር መጋባት ይኖርብሻል”፡፡

FeedBurner FeedCount