Showing posts with label ጌታ ሆይ አምናለሁ -የዮሐንስ ወንጌል የ40ኛ ሳምንት ጥናት. Show all posts
Showing posts with label ጌታ ሆይ አምናለሁ -የዮሐንስ ወንጌል የ40ኛ ሳምንት ጥናት. Show all posts

Tuesday, October 30, 2012

ጌታ ሆይ አምናለሁ -የዮሐንስ ወንጌል የ40ኛ ሳምንት ጥናት (ዮሐ.9)


       በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
  በምዕራፍ 8 እንደተመለከትን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚነግራቸውን ነገር ከማመን ይልቅ አይሁድ “ጋኔን አለብህ” /8፡48/ ብለው በድንጋይ ሊወግሩት ሽተው ነበርና አንድም “አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ” /8፡58/ ብሏቸው ነበርና ቁጣቸውን አብርዶ ቀዳማዊነቱን በገቢር (በሥራ) ያስረዳቸው ዘንድ ወደደ /መዝ.51፡4/፡፡ ስለዚህም ሲያልፍ ከመወለዱ ጀምሮ ዕውር የሆነውን ሰው (ሲለምን) አየ /ቁ.1/። ይህ ዐይነ ሰውር ሰው የዓይን ምልክት እንኳን አልነበረውም፡፡ እንዲሁ ልሙጥ ግንባር ነበረው እንጂ፡፡ ስለዚህ ሰውዬው ሳይሆን ክርስቶስ አየው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ክርስቶስ ዕዉሩን በልዩ እይታ (በፍቅርና በሐዘኔታ) እንዳየው አስተዋሉ፤ ደነቃቸውም፡፡ አስቀድሞ መጻጉዑን ሲፈውሰው፡- “ዳግመኛ እንዳትበድል” ብሎት ስለነበረ /5፡14/ “ይህ ዕዉር ሆኖ የተወለደውም ዕዉርነቱ ከበደል የተነሣ ነው ማለት ነው” ብለው አሰቡ፡፡ አሳባቸው ግን ግራ አጋባቸው፡፡ ስለዚህም፡-  መምህር ሆይ፥ ይህ ሰው ዕውር ሆኖ እንዲወለድ ኃጢአት የሠራ ማን ነው? እርሱ ነው ወይስ ወላጆቹ?” ብለው ጌታን ጠየቁት /ቁ.2/። ጌታችንም፡-እርሱ ወይም ወላጆቹ ኃጢአት አልሠሩም፡፡ ምክንያቱም እያንዳንዱ ሰው በራሱ ኃጢአት ይቀጣል እንጂ አባት ስለ ልጅ ልጅም ስለ አባት አይቀጣምና /ዘዳ.24፡16/፡፡ ታድያ እርሱ ነውን? ብትሉም አይደለም እላችኋለሁ፡፡ እንግዲያ ስለምን ዓይነ ስውር ሆነ? ብትሉም የእግዚአብሔር ሥራ (አስቀድሞ አዳምን ከምድር አፈር የፈጠርኩት ቀዳማዊ የምሆን እኔ መሆኔን) በእርሱ እንዲገለጥ ነው እላችኋለሁ /St. Ephrem the Syrian, Commentary on Tatation’s Diatessaron, 28 /፡፡

FeedBurner FeedCount