Saturday, May 19, 2012

የእግዚአብሔር በግ (የዮሐንስ ወንጌል የ7ኛው ሳምንት ጥናት)!!

“በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ። እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።” ዮሐ.1፡29
 የሚገርም ምስክርነት ነው፡፡ ጌታስ “በሰው ፊት የሚያምንብኝን ሁሉ እኔም በእግዚአብሔር መላእክት ፊት አምነዋለሁ” አይደል ያለው /ሉቃ.12፡8/፡፡ መጥምቁ ምስክርነቱን ለአይሁድ ሁሉ ላንቃው እስኪሰነጠቅ ድረስ “ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ዘያአትት ወያሴስል ኃጢአተ ዓለም- የሰውን ኃጢአት የሚያስተሰርይ የእግዚአብሔር መሥዋዕቱ እነሆ!” ይላቸው ነበር /John Chrysostom, Homily on the Gospel of John, 17/፡፡ አዎ! ዮሐንስ ከእንግዲህ ወዲህ ዝግጅቱን ጨርሷል፡፡ ያ ለስድስት ወራት ሲያዘጋጀው የነበረና ለዓለም ሁሉ የሚሠዋው ንጹሑ በግ መጥቷልና /2ቆሮ.5፡14፣ ቅ.ቄርሎስ ዘአሌክሳንድርያ Commentary on the Gospel of John 2:1/፡፡ ይህ ንጹሕ በግ እንደ ብሉይ ኪዳኑ ዓይነት በግ አይደለም፤ ይህ በግ ነብዩ “እኔም ለመታረድ እንደሚነዳ እንደ የዋህ በግ ጠቦት ሆንሁ” ያለው ነው /ኤር.11፡29፣ አርጌንስ Commentary on the Gospel of John 6/፡፡ ይህ በግ ኢሳይያስ “በሸላቾቹ ፊት ዝም አለ” ያለለት በግ ነው /ኢሳ.53፡7፣ አውሳብዮስ ዘቂሳርያ Proof of the Gospels 1:10/፡፡ ይህ በግ በዕጸ ሳቤቅ (በእመቤታችን) ተይዞ የተገኘውና በይስሐቅ ፈንታ የተሠዋው በግ ነው /ዘፍ.22፡13፣ አውግስጢኖስ Sermon 19:3/፡፡ ይህ በግ በምድረ ግብጽ ሞተ በኩር በመጣ ጊዜ በእስራኤላውያን በኩራት ፈንታ የተሠዋው በግ ነው /ዘጸ.12፡21-30/፤ ይህ በግ አቤል ለእግዚአብሔር ያቀረበው ንጹሑ በግ ነው /ዘፍ.4፡4፣ አምብሮስ/፡፡
 መጥምቁ በዚያ ለነበሩ አይሁድ ይህን ሁሉ የሚመሰክርላቸው በመጻሕፍቶቻቸው የተነገረውን ትንቢት ሁሉ መፈጸሙን አውቀው በክርስቶስ እንዲያምኑ ነው /ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒ ከማሁ/፡፡
 የሚደንቅ ነው! ይስሐቅ ከርብቃ ጋር /ዘፍ.24/፣ ያዕቆብ ከራሄል ጋር /ዘፍ.29/፣ ሙሴም ከሲፓራ ጋር ለመጋባት በውኃ ጉድጓድ እንደተገናኙ ሁሉ /ዘጸ.2፡15-21/ ክርስቶስም ከሙሽራው ከቤተ ክርስቲያን ጋር በዮርዳኖስ ወንዝ ተጋብቷል /ኤፌ.5፡32፣ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ Commentary on Tatians Diatessaron 3:17/፡፡
 መጥምቁ ምስክርነቱን ይቀጥልና “አንድ ሰው ከእኔ በኋላ ይመጣል፥ ከእኔም በፊት ነበርና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል ብዬ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነው።” ይላቸዋል /ቁ.30/፡፡ እንዲህ ማለቱ ነበር፡- “የዓለምን ኃጢአት ያስወግዳል ያልኳችሁ በግ፣ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል ያልኳችሁ ሰው እርሱ ነው፡፡ እርሱ አወጣጡ ከዘላለም የሆነ አምላክ ነው፤ እኔ ግን አይደለሁም፡፡” አሁንም ይቀጥልና “እኔም አላውቀውም ነበር” ይላል/ቁ.31/፡፡ “ታድያ ካለወቅከው እንዴት ትመሰክራለህ? ካላችሁኝም ‘አላውቀውም ነበር’ አልኳችሁ እንጂ ‘አላውቀውም’ አላልኩም ብዬ እመልስላችኋለሁ፡፡ ‘አወጣጡ ከዘላለም ከሆነ ታድያ አሁን ካንተ ዘንድ ለመጠመቅ ምን አተጋው?’ ካላችሁኝም እንዲህ እላችኋለሁ ‘ለእስራኤል ይገለጥ ዘንድ ስለዚህ በውኃ እያጠመቅሁ እኔ መጣሁ’ ብዬ እመሰክራችኋለሁ፡፡ እርሱስ እንደ እኔና እንደናንተ ጥምቀት የሚያስፈልገው አይደለም፡፡ ‘ቅድም አላውቀውም ነበር ብለኸን ነበር፡፡ አሁን እንዴት አወቅከው?’ ካላችሁኝ ‘መንፈስ ከሰማይ እንደ ርግብ ሆኖ ሲወርድ አየሁ፤ በእርሱ ላይም ኖረ። እኔም አላውቀውም ነበር፥ ዳሩ ግን በውኃ አጠምቅ ዘንድ የላከኝ እርሱ፡- መንፈስ ሲወርድበትና ሲኖርበት የምታየው፥ በመንፈስ ቅዱስ የሚያጠምቅ እርሱ ነው አለኝ’ እላችኋለሁ” /ቁ.32-33/፡፡  መጥምቁ እየደጋገመ “አላውቀውም ነበር” የሚለን ስለ ክርስቶስ የሚሰብከው ሁሉ “ተዛምዶተ ሥጋ ኑሮት ነው፤ ማማለጃ ተቀብሎ ነው፤ አብሮ አደግ ሁኖ ነው” ብሎ ማንም እንዳያስብ ነው፡፡ በበረሀ የማደጉ አንዱ ምሥጢርም ይኸው ነበር /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒ ከማሁ/፡፡
 የመንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል መውረድ ሌላ የሚያስገነዝበን ምሥጢር አለው፡፡ ይኸውም እንዲህ ነው፡- መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን ሰው በእግዚአብሔር መልክ እና ምሳሌ  ተፈጥሯል፡፡ እግዚአብሔር ሰውን ከአፈር ካበጃጀው በኋላ እፍ ሲልበት መልኩን ሥሎበታል፡፡ ሲበድል ግን ይህ መልኩ ተበላሽቷል፤ የጸጋ ልብሱ ቆሽሾአል፡፡ የተሰጠው መንፈስ ቅዱስ እየራቀው ሄደ፡፡ ፈጣሪውንም እየረሳ ሄደ፡፡ መፍቀሬ ሰብእ እግዚአብሔር ግን የተበተነውን መንጋ መሰብሰብ ወደደ፡፡ የሰው ልጅ በመጀመርያው አዳም ያጣውን ጽድቅም በሁለተኛው አዳም መታዘዝ የእግዚአብሔር ቤተ ሰብእ አደረገው /2ቆሮ.5፡21/፡፡ መንፈስን የሚያድል ክርስቶስም ከእኛ ርቆ የነበረውን ቅዱስ መንፈስ በእኛ ተገብቶ ተቀበለው፡፡ በኃጢአታችን ምክንያት የራቀው መንፈስ ቅዱስ በክርስቶስ ንጽሕና ወደ እኛ ተመለሰ /ቅ.ቄርሎስ ዘአሌክሳንድርያ፣ ዝኒ ከማሁ/፡፡ በኖኅ ጊዜ እንደተደረገውም ያ መንፈስ ቅዱስ ለቤተ ክርስቲያን ሰላም ሲያውጅ ተመልክተናል /ቅ.ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም፣ Catechetical Lecture 17:9/፡፡
 ከእናንተ መካከል “አይሁድ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ሲወርድ እየተመለከቱ እንዴት በክርስቶስ አላመኑም?” ብሎ የሚጠይቅ ሊኖር ይችላል፡፡ እኔም እንዲህ ብዬ እመልስለታለሁ፡- “ነገረ እግዚአብሔር በዓይነ ሥጋ ብቻ በማየት አይገባም፤ ይልቁንም በዓይነ ልቡና አይቶ ማስተዋልን ይጠይቃል እንጂ” /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒ ከማሁ/፡፡
መጥምቁ ንግግሩን እንዲህ ብሎ ይጨርሳል፡- “እኔም አይቻለሁ-  ከመ ዝንቱ ውእቱ ወልዱ ለእግዚአብሔር- እርሱ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ እንደ ሆነ መስክሬአለሁ” /ቁ.34/፡፡
እውነት ነው!! ሁላችንም ክርስቶስ እርሱ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ እንደሆነ፤ በአንድነት በሦስትነት የሚመሰገን አምላክ እንደሆነ፤ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዳለው፤ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቁጣ በእርሱ ላይ እንደሆነች ልንመሰክር ያስፈልጋል፡፡ ይህን ሁሉ በአፍም በመጣፍም እንዲሁም በምግባር እንገልጠው ዘንድ ሰውን በመውደድ ሰው የሆነው ክርስቶስ ይርዳን አሜን!!!

የዮሐንስ መጥምቅ ምስክርነት (የዮሐንስ ወንጌል የስድስተኛው ሳምንት ጥናት)!!

“አይሁድም አንተ ማን ነህ? ብለው ይጠይቁት ዘንድ ከኢየሩሳሌም ካህናትንና ሌዋውያንን በላኩበት ጊዜ፥ የዮሐንስ ምስክርነት ይህ ነው” /ቁ.19/፡፡  ቅናት ክፉ ነገር ነው፡፡ ክፋትነቱም ለአድራጊው እንጂ ለሚደረግበት ሰው አይደለም፡፡ ሐዋርያውስ፡-“ብትበደሉ አይሻልምን? ብትታለሉስ አይሻልምን?” አይደል ያለው /1ቆሮ.6፡7/? ወንጌላዊው እነዚህ አይሁድ ከየት እንደመጡ የሚነግረን ያለምክንያት አይደለም፡፡ ከዋናው ቤተ መቅደስ የመጡ እጅግ ክፉዎች መሆናቸውን ለመናገር እንጂ፡፡ ዮሐንስ ማን መሆኑን እማ “ይህ ሕጻን ምን ይሆን” እያሉ ሲደነቁ ነበርና /ሉቃ.1፡66፣ St. John Chrysostom homily on the Gospel of John, homily 16/፡፡ ተራው ሕዝብ ግን መጥምቁ በሚናገረው ሁሉ በጣም ስለሚማረኩ በቀላሉ የሚለውን ሁሉ ያምኑት ነበር፡፡ ስለዚህም ራሱን ከፍ ከፍ ለማድረግ ዕድል ነበረው፤ “አዎ መሲሑ ነኝ” ቢላቸው እንኳን ባላንገራገሩ ነበር፤ አላደረገውም እንጂ /Augustin sermon 289:4/፡፡ ካህናቱና ሌዋውያኑ ግን አይቀበሉትም፡፡ በእውነትም የእፉኝት ልጆች ናቸው፡፡ ወደ ወንዙ እየመጡ ሲጠመቁ የነበሩ ሰዎች አሁን ከሕዝቡ የሚቀበሉትን ከበሬታ ስለቀነሰባቸው “ማን ነህ” ይሉት ጀመር፡፡ ብጹዕ ዮሐንስ ግን ተራው ሕዝብ “መሲሑ ሊሆን ይችላል” የሚለውን የተሳሳተ ግንዛቤአቸው ለማቅናት ሳይክድ “እኔ ክርስቶስ አይደለሁም” ይላቸው ነበር፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን የእነዚህ ክፉ እረኞች ምክንያታዊነትም ከንቱ ለማድረግ ወንጌላዊው “ዮሐንስ መሰከረ” እያለ ሦስት ጊዜ ይነግረናል /ቁ.8፣ 15፣ 20/፡፡
 ከዚያ በኋላ ወደ ሌላ ጥያቄ ያመሩና፡- “እንኪያስ ማን ነህ? ኤልያስ ነህን?” ይሉታል /ቁ.20/፡፡ ምክንያቱም ከመሲሑ በመቀጠል በጉጉት የሚጠብቁት ኤልያስ ነው፡፡ ነገር ግን ምንም እንኳን ኤልያስ የዳግም ምጽዓት አዋጅ ነጋሪ በመሆን ከዮሐንስ ጋር ቢመሳሰልም “እኔ ኤልያስ አይደለሁም” ይላቸው ነበር /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒከማሁ/፡፡
 ምናልባት ከእናንተ መካከል ጌታ፡- “`ኤልያስስ መጥቷል` ካለው ጋር አይጋጭምን?” ብሎ የሚጠይቅ ሰው ሊኖር ይችላል /ማቴ.17፡10/፡፡ በፍጹም! ምክንያቱም ቅዱስ ገብርኤል ይህንን ሐሳብ ግልጽ ሲያደርግልን “እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ… በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል” ብሎናል /ሉቃ.1፡17/፡፡ ይህም ማለት “ዮሐንስ በኤልያስ መንፈስ መጣ እንጂ በቁሙ ኤልያስ አይደለም” ማለት ነው፡፡ እውነት ነው! ኤልያስ የዳግም ምጽዓት አዋጅ ነጋሪ እንደሆነ ሁሉ በኤልያስ መንፈስ የመጣው ዮሐንስም ለመጀመርያው ምጽዓት አዋጅ ነጋሪ ነበርና /Gregory the Great, Forty Homelies, 4/፡፡
  አሁንም ይቀጥሉና፡- “ታድያ ኤልያስ ካልሆንክ በኦሪት ዘዳግም ሙሴ ይመጣል ያለው ነብዩ ነህን?” ብለው ለሦስተኛ ጊዜ ይጠቁታል /ዘዳ.18፡15፣ Origen: commentary on the Gospel of John/፡፡ እርሱ ግን “ነብይ አይደለሁም” ሳይሆን “እናንተ የምትሉት ነብይ አይደለሁም” ይላቸው ነበር /ማቴ.11፡9፣ ታላቁ ጐርጐርዮስ ዝኒ ከማሁ/፡፡
 የሚገርመው ግን እነርሱም ጥያቂያቸውን ሳይሰለቹ ይጠይቁታል እርሱም ሳይሰለች ይመልስላቸዋል /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒ ከማሁ/፡፡ “እንኪያስ ማን ነህ? ለላኩን መልስ እንድንሰጥ፤ ስለራስህ ምን ትላለህ? አሉት” /ቁ.22/፡፡ እርሱም በሕዝቡ ልቡና ያለውን የተሳሳተ ግንዛቤና በእነዚያ ያለውን ተንኰል ከንቱ ካደረገ በኋላ እነርሱ ከሚቀበሉት መጽሐፍ እየጠቀሰ፡- “እኔ በበረሀ የሚጮህ ድምጽ ነኝ፤ ከእኔ በፊት የነበረውና አሁን ሥጋ ለብሶ በመካከላችሁ የቆመው ቃል ግን የምትጠብቁት መሲሕ ነው” እያለ የነቢዩ ኢሳይያስን የትንቢት ፍጻሜ ይነግራቸው ነበር /ቁ.23፣ ኢሳ.40፡3፣ ታላቁ ጐርጐርዮስ ዝኒ ከማሁ 6/፡፡ እንዲህ እያደረገም ልቡናቸውን የንስሐ ፍሬ አፍርቶ ለጌታ እንዲያዘጋጁ አጥብቆ ያስተምራቸው ነበር፤ ሁሉም እንዲሰሙትም ጮክ ብሎ ይናገር ነበር፤ ከእግዚአብሔር ጸጋ ተራቁታ የነበረችው ነፍስ ከአምላኳ ጋር እንድትገናኝ ያዘጋጅ ነበር /አርጌንስ ዝኒ ከማሁ 6፡100/፡፡
 “የተላኩትም ከፈሪሳውያን ነበሩና። እንኪያስ አንተ ክርስቶስ ወይም ኤልያስ ወይም ነቢዩ ካይደለህ፥ ስለ ምን ታጠምቃለህ? ብለው ጠየቁት” /ቁ.24/፡፡ አስቀድመን ቅናት ያልነው እንግዲህ ይኸው ነው፡፡ ምክንያቱም መጥምቁ ማንነቱን በትክክል እየነገራቸው እንኳን ይሰናከሉበት ነበርና /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒከማሁ/፡፡ ዮሐንስ ግን የእርሱ ጥምቀት በኢየሱስ ክርስቶስ ለምትመጣው ፍጽምት ጥምቀት የማዘጋጀት አገልግሎት እንደሆነች “እኔ በውኃ የንስሐ ጥምቀት አጠምቃለሁ፤ ዳሩ ግን እናንተ የማታውቁት ልጅነትን በምታሰጥ ጥምቀትም የሚያጠምቅ በመካከላችሁ ቆሞአል” እያለ ይነግራቸው ነበር /St. Cyril of Alexandria Commentary on the Gospel of John 1:10/፡፡ በእርግጥም የዮሐንስ ጥምቀት ለንስሐ የምታዘጋጅ እንጂ መንፈስ ቅዱስን የምታሰጥ አልነበረችም /ታላቁ ጐርጐርዮስ ዝኒከማሁ 4 /፡፡
 እነዚህ ክፉዎች ይዘውት ለመጡት ተንኰልና በሕዝቡ ልብ የነበረውን የተሳሳተ ግንዛቤ በመቃወምና በጣቱ እያመለከተ፡- “እነሆ እናንተ በመለኰቱ አይታችሁት የማታውቁ አሁን ሥጋ ለብሶ በእናንተ መካከል አለ፤ እርሱ በመጀመርያ ቃል የነበረ ነው፤ አሁን ግን በምልዓት ያልተለየውን ዓለም ሥጋ ለብሶ ጎብኝቶታል፤ እርሱ ከእኔ ይበልጣል፤ እኔ ግን የጫማውን ጠፍር እንኳን መፍታት የማይገባኝ ወራዳ ነኝ፤ ዮሐንስ ይበልጣል የሚለው የተሳሳተ ግንዛብያችሁ አስወግዱና ከእኔ ይልቅ ወደ እርሱ ዘወር በሉ፤ እኔ ሚዜ ነኝ እርሱ ግን ሙሽራ ነው” እያለ ለሁሉም ይመልስላቸው ነበር /Apolinaris of Laodicea, Fragments on John 5/፡፡ በጥንት ጊዜ፥ ማንም ቢሸጥ ቢለውጥም፥ ነገሩን ለማጽናት ሰው ጫማውን እንዲያወልቅ ለባልንጀራውም እንዲሰጠው በእስራኤል ዘንድ ልማድ ነበረ /ሩት.4፡7/፡፡ ሙሽራይቱ (ቤተ ክርስቲያን) ያለችው ደግሞ እርሱ ክርስቶስ እንጂ ዮሐንስ አይደለም፡፡ ስለዚህ መጥምቁ “እንኳንስ ሙሽራ ልሆን ቀርቶ እርሱ የረገጣትን ኮቴ እንኳን ልረግጥ አይገባኝም” ማለቱ ተገቢ ነበር /ታላቁ ጐርጐርዮስ ዝኒከማሁ 4/፡፡
 ይህ ሁሉ በሰዋራ ቦታ ሳይሆን ሕዝቡ በተሰበሰበበት ዮሐንስም ያጠምቅበት በነበረው በዮርዳኖስ ማዶ በቢታንያ እና በቤተ ራባ ሆነ /ቁ.28፣ ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒ ከማሁ/፡፡
 ወንድሞቼ! ሴቶች ከወለዷቸው ሁሉ ከእርሱ የሚበልጥ የሌለ ዮሐንስ የጌታን የጫማ ማዘብያ መንካት አይገባኝም ካለ እኛማ ምን ያህል ያልተገባን እንሆን ይሆን? ዓለም ለእርሱ ያልተገባችው ይልቁንም ዕድሜውም በሙሉ እግዚአብሔርን በማገልገል አንገቱ የተሰየፈው ዮሐንስ እንዲህ ካለ በኃጢአት የጨቀየን እኛማ ምን እንል ይሆን? ትሕትናው እንዴት ከፍ ከፍ እንዳደረገችው ታስተውሉ ዘንድ እማልዳችኋለሁ! እርሱ የጫማውን ማዘብያ እንኳን “አልነካም” ቢልም ሰውን አፍቃሪ ጌታ ግን “እንኳንስ ጫማዬ ገና እኔን ታጠምቀኛለህ” ብሎታል፤ “አጥምቆታልም”፤ ጴጥሮስም “ጌታ ሆይ እኔ ኃጢአተኛ ነኝና ከእኔ ራቅ” ቢለውም ሰው ወዳጁ ጌታ ግን “ገና ቤተ ክርስቲያኔን በአንተ ላይ እመሠርታታለሁ” ብሎታል፡፡ እውነት ነው! ትዕቢት ቅዱሳን መላእክትን ርኩሳን መላእክትን ታደርጋለች፤ ትሕትና ግን ወደ ሕይወት ዛፍ የምታስወጣ መሰላል ነች፡፡ ምንም ያህል ጾመኞች፣ ጸሎትን የምናዘወትር፣ ሌላም ሁሉ ብናደርግ ትሕትና ግን ከሌለን የትሕትና ጌታ ከእኛ ጋር የለም፡፡ በሰው ዘንድ ከፍ ከፍ ያለ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን የረከሰ ነውና /ሉቃ.16፡15/፡፡ አቤቱ እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደ በደላችን አይሁን፡፡ አሜን!!  

Friday, May 18, 2012

THE MOST VERSATILE ETHIOPIAN SCHOLAR & SAINT- St. YARED=+=



IN THE NAME OF THE FATHER, THE SON, AND OF THE HOLY SPIRIT ONE GOD AMEN!

Selam=+= (To mean Peace be to you in Ethiopic!)

Here is the second part of what I have promised you in the last time.
St. Yared; the great Ethiopian scholar, was born in Axum (One of the Ancient Cities in the world in Northern Part of Ethiopia and where the Arc of the Covenant lies) in 505 AD (This is Ethiopic calendar. I will present in the future). His father was called Isaac and his mother Christina.

His father died when he was 7. His mother then gave to the then Scholar and his uncle; Gedewon, in the courtyard of Axum Zion church to adopt her son and to take over the responsibility regarding his education. But; St. Yared was not intelligent enough in the beginning to compete with the other children, and His uncle was so impatient with him and he gave him several lashes for his inability not to compete with his peers.
Realizing that he was not going to be successful with his education, Yared left school and went to Medebay, a town where his another uncle resided. On his way to Medebay, not far from Aksum, he was forced to seek shelter under a tree from a heavy rain, in a place called Maikrah. While he was standing by leaning to the tree, he was immersed in thoughts about his poor performance in his education and his inability to compete with his peers. Suddenly, he noticed an ant, which tried to climb the tree with a load of a seed. The ant carrying a piece of food item made six attempts to climb the tree without success. However, at the seventh trial, the ant was able to successfully climb the tree and unloaded the food item at its destination. Yared watched the whole incident very closely and attentively; he was touched by the determined acts of the ant. He then thought about the accomplishment of this little creature and then pondered why he lacked patience to succeed in his own schooling.

He got a valuable lesson from the ant. In fact, he cried hard and then underwent self-criticism. The ant became his source of inspiration and he decided to return back to school. He realized the advice he received from his uncle was a useful advice to guide him in life. He begged Aba Gedeon to forgive him for his past carelessness. He also asked him to give him one more chance. He wants all the lessons and he is ready to learn.

His teacher, Aba Gedewon then began to teach him the Book of David. Yared not only was taking the lessons, but every day he would stop at Aksum Zion church to pray and to beg his God to show him the light. His prayer was answered and he turned out to be a good student. Within a short period of time, he showed a remarkable progress and his friends noticed the change in him. They were impressed and started to admire him. He completed the Old and New Testaments lessons at a much faster pace. He also finished the rest of lessons ahead of schedule and graduated to become a Deacon. He was fluent in Hebrew and Greek, apart from Ge’ez. After that he become a Deacon & served at Axum Zion Church where he late on become a married priest who succeeded to the position of his uncle. He was the first Ethiopian Scholar to compose a hymn. But his hymn was not a result of learning only; but a matter of inspiration. As a matter of inspiration, he was made to enjoy the company of, and listening to the singing of angels (which revealed themselves in the form of three birds!) and then he was taken up in spirit to the heavenly Jerusalem where he could learn the song of the Twenty Four Priests to heaven. When he returned to himself, he went into the church of Axum at the 3rd hour of the day & he began to cry out with a loud voice saying “hale luya laab, hale luya lewold, hale luya wolemenfes qidus qidameha letsion semaye sarere wedagem arayo lemusse zekeme yegeber gibra ledebtera which is to mean Hallelujah to the Father, Hallelujah to the Son, Hallelujah to the Holy Spirit.’’ This was later labeled Mahlete Aryam (The Highest).

His hymn has three modes: Geez, Araray, and Ezil. These three modes are well characterized in a way, which can be used on fast days, ordinary days, and on great festivals.
His literature has unique mystery in his hymnary (In Ethiopic Digwa). He arranged hymns for each season of the year; for summer, winter, spring, and Autumn, and for festivals and Sabbaths, and for the days of St. Mary, Angels, the Prophets, the Martyrs, the Apostles and the Righteous.

St. Yared preached the Gospel throughout Ethiopia. He also composed a song to the Ethiopian Anaphora. There are five hymn books composed by St. Yared. They are: Digwa, Tsome Digwa, Mieraf, Zimare,Mewasiet, and The Chant of the Liturgy.He used to elaborate his hymn in musical notation which in many ways is connected with its religious meaning (symbol). It consists of Biblical signs and letters as well as musical dots placed above the relevant syllables. They indicate the raising or lowering of the voice as well as other modes of pronunciation.

These Signs (Milikt in Ethiopic) serve to instruct the singer in how to instruct the single note and how to interpret the melody (Note that Mozart was not yet born).
The signs are 8. (It is difficult for me to put them here in sign as am not good in drawing! But; you can easily Google it.)

In general the works of Yared would consolidate almost the Theological, Ethical, Musical and Philospphical world of human thought (Qine- to mean Poet in Ethiopic).

St. Yared is the most venerated Holy Father canonized by the church and a great Theologian who could help the Christian Faith to be deeply rooted in the country. The bad news is his writings are not yet translated to other international languages.

The feast of St. Yared is tomorrow, Ginbot 11 E.C. (which is 19th of May in. G.C.).

May the blessings and Intercession of St. Yared be with us and all Christians. Amen!!
(To be continued in other Ethiopic articles)

=+=ድንግል ማርያም በቅ/ገብርኤል ሠላምታ (ክፍል ሁለት)=+=በመምህር ቃለአብ ካሳዬ=+=


ያለፈው ክፍል
ድንግል ማርያም በቅ/ገብርኤል ሠላምታ (ክፍል 1)

አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ

            ይህን የመልአኩን ቃል ቅ.ኤልሣቤጥም ሳትጨምር ሳትቀንስ ደግመዋለች (ሉቃ 1.47)። የድንግል ማርያም ከሴቶች ሁሉ ተለይቶ መባረክ በቅ.ገብርኤልና በቅ.ኤልሳቤጥ መመስከሩ ይህ እውነት በሠማይና በምድር የጸና መሆኑን ያሳያል። ገብርኤል ከሰማይ ኤልሳቤጥ ከምድር ለሆኑት ወኪል ናቸውና።

     አንዳንዶች ከሴቶች መካከል ማለት “እንደሴቶች ሁሉ” ወይም “ከእነርሱ እንደ አንዱ” ማለት ነው። ከዚህ ውጭ “ ተለይታ” የሚል ሐረግ ባለመኖሩ ከአማኞች ጋር የምትቆጠር አንድ ተራ ግለሰብ ናት ብለዋል። ታድያ እንደሌሎች ሴቶች ከሆነች ሌሎች ሴቶች ይህን ብሥራት ለምን አንደ እርሷ አልተቀበሉም?

  ከሴቶች ተለይታ የመባረኳ ምስጢር:-

  • ሌሎች ሴቶቸ ቢወልዱ፣ ፃደቃን ሰማዕታትን ነው ፣እርሷ ግን የወለደችው የእነርሱን ጌታ ነው።
  • ሌሎች ድንግል ቢሆኑ እስከጊዜው ነው፣ኋላ ተፈትሆ/ድንግልናን ማጣት/አለባቸው። እርሷ ግን በጊዜው ሁሉ ድንግል ናት።
             በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ እንዲህ የሚል ጽሑፍ አለ:-“እነዚህ ሁሉ ከሴቶችና ከኢየሱስ እናት ከማርያም ከወንድሞቹም ጋር በአንድ ልብ ሆነው በፀሎት ይተጉ ነበር።” (ሐዋ 1፡14) ጸሐፊው ሐዋርያው ሉቃስ የኢየሱስ እናት እንደሌሎች ሴቶች ብትሆን “ ከሴቶች ጋር” ይል አልነበረምን? ከሴቶችተለይታ የተባረከች በመሆኗ ግን “ ከሴቶችና ከኢየሱስ እናት” ብሎ ለይቶ ፃፈ።

አርሷም ባየቸው ጊዜ ከንግግሩ በጣም ደነገጠቸና ይህ አንዴት ያለ ሠላምታ ነው ብላ አሰበች ድንጋጤ የህሊና ፤ ፍርሃት የልቦና፣ ረዓድ የጉልበት ነው። ድንግል ማርያም የደነገጠችው ከመልአኩ ንግግር የተነሳ በመሆኑ“ ከንግግሩ በጣም ደነገጠችና” የሚል ቃል እናነባለን። የተነገረን ቃል ሁሉ እንደወረደ መቀበል ከቶ መንፈሳዊነት አይደለም። ይልቁንም“ይገባኛል ወይ?”   ማለት ይገባናል። በደነገጡበት ሰዓት ማሰብ ከባድ ቢሆንም ድንግል ማረያም ግን “ ……ብላ አሰበች” ይላል። ድንጋጤ የህሊና ነዉና በህሊናዋ ጠየቀች ማለት ነዉ።  እንግዲያውስ ድንጋጤዋ ከእምነት ማነስ ሳይሆን “እንዴት ያለ ሰላምታ ነው?” ከሚል ጥልቅ መገረም ነው። የሚገባትን የክብር ሰላምታ ቆም ብላ ከመረመረችው፣ የማይገባቸውን ምስጋና  ሳይመረምሩ ለሚቀበሉ፣ በአሚና ዝማሬ በደብተራ ቅኔ ለሚኮፈሱ ይህ ተግሣጽ  ነው።!

 መልአኩም እንዲህ አላት፡- ማርያም ሆይ በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ አግኝተሻልና አትፍሪ!

ፍርሃት አርቆ መናገር ለመልአክ አዲስ ባለመሆኑ ሲሆን ዋናው ግን ነደ እሳትን ብሩህ መለኮትን ትሸከሚያለሽና አትፍሪ ሲላት ነው።

እነሆም ትፀንሻለሽ፣ ወንድ ልጅም ትወልጂያለሽ፣ ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ !

ጸንሳ ወንድ ልጅ መውለዷ ቀድሞም በትንቢት በሰፊው ተጠቁሟል። (ት.ኢሳ.7፡14) (ት.ኢሳ 9/6)። መልአኩ ግን የዚህ ወንድ ልጅ ስሙ ኢየሱስ መሆኑን ነገራት። ኢየሱስ ማለት “መድሃኒት” ማለት ነው። መድሃኒትነቱ ለ^ጢአትም፣ ለሞትም ነው! ይህን ስም ተሸክሞ ታምሞ  የማይታከም፣ ሞቶ የማይነሳ ማንም የለም!

   ኢየሱስ የሚለው ክቡር ስሙ
  •  ከስም ሁሉ በላይ የሆነ (ፊሊ 2፡10)
  • ከሰማይ በታች እንድንድንበት ዘንድ የተሠጠ ( ሐዋ4፡12)
  • ጉልበት ሁሉ የሚሰግድለት (ፊሊ 2፡10)
  • ምላስ ሁሉ የሚመሰክርለት (ፊሊ2፡11)
  • ተጠርቶ የሚለመን (ዮሐ14፡14)
  • የ^ጢአት ሥርየት የሆነ (ሐዋ2.38) (ሐዋ3፡16)
  •  ብዙ መከራ የሚጠራ (ማቴ 5፡11)
  • ዘወትር የምናጌጥበት (ራዕ7:5)
  • እንዲሁም የሚያጸድቀን ነው (ሮሜ 10፡13)
እርሱም ታላቅ ይሆናል! የልዑል ልጅ ይባላል።

አርሱም ታላቅ ይሆናል:- እርሱ ቀድሞም ታላቅ ነው! ተንቆ የነበረው የእኛን ማንነት ሲዋሐድ ያገኘነውን ክብር ለመግለጽ ግን ታላቅ ይሆናል አለ!
የልዑል ልጅ ይባላል:- እርሱ ቀድሞም የልዑል ልጅ ነው፣ እርሱ የሰው ልጅ ሲሆን፣እኛም የልዑል ልጆች መሆናቸንን አረጋገጠልን። እርሱ እኛ ጋር ሲሆን እኛም እርሱ ጋር ሆነናልና ከራሱ ጋር ይጠራናል!

ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋነ ይሰጠዋል!

 የዳዊትን ዙፋን የማይሻ ፣የእሳት ዙፋን ጥሎ የመጣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል ማለት አብ ክርቶስን የዳዊትን ሥጋ ያዋሕደዋል ማለት ነው። ክርሰቶስ በዳዊት ሥጋ የዳዊት ልጅ ነውና። አብ በማዋሐድ ፣ ወልድ በመዋሐድ፣ መንፈስ ቅዱስ በማጽናት በድንግል ማርያም ረቂቅ ሥራ ተፈጽሟል። መዝ (88)
በያዕቆብ ቤትም ለዘለዓለም ይነግሳል

       ያዕቆብ አስራኤል ተብሏል (ዘፍ 32:22)። ኢየሱስ ክርስቶስ በእስራኤል
       ዘሥጋ ለጊዜው በትንቢት፣ በእስራኤል ዘነፍስ  (በክርስቲያኖች) ላይ ግን በፍቅር    
       ለዘለዓለም ነግሷል።
      ለመንግሰቱም መጨረሻ የለውም

ይህ ቃል አሰቀድሞ በነቢዩ በዳንኤል “በወገኖችና አሕዛብ ላይ ልዩ ቋንቋም  የሚናገሩ ሁሉ ይገዙለት ዘንድ ግዛትና ክብር መንግስትም ተሰጠው፣ ግዛቱም የማያልፍ የዘለዓለም ግዛት ነው። መንግስቱም የማይጠፋ ነው”። ተብሎ ተነግሯል (ት.ዳን 7፡13-14)

ማርያምም መልአኩን ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል? አለችው።

በአካልም በአሳብም ወንድ የማታውቅ መሆኗን የሚያሳይ የከበረ ቃል ነው።እኔ አንዱንም ሳላሰብ አንተ ብዙ ነገረ አልከኝ፣ ምድር ያለ ዘር፣ ሴት ያለወንድ ዘር እንዴት ይሆናል? አለችው “ እንዴት?” ስትል መልአኩ እንደካህኑ ዘካርያስ አልገሠፃትም! ምክንያቱም:-

    1ኛ. ካህኑ ዘካርያስ ካረጀሁ በኋላ እንዴት አወልዳለሁ? ቢል ካረጀ በኋላ የወለደ
      አባቱ አብርሃም ነበረና ማመን ይገባው ነበር። ድንግል ማርያም ግን
      በድንግልና ወልዶ የታየ ምሳሌ የሌላት ከመሆኑም ባሻገር ይህ ነገር
      ከመልአኩ ዕውቀት በላይ በመሆኑ ነው።
     2ኛ. መልአኩ በፊቱ ቆሞ  የሚያገለግለውን ጌታ እርሷ ወልዳው ያገለግላታልና በማዕረግ ጉዳይ ያከብራታል (ሉቃ 1፡19)  (ሉቃ2፡51)።

  “መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፣ የልዑልም ^ይል ይጸልልሻል፣ ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል፣ እነሆ ዘመድሽ ኤልሣቤጥ እርሷ  ደግሞ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ጸንሣለች። ለእርስዋ መካን ትባል ለነበረችው ይህ ሰደስተኛ ወር ነው።”

የመልአኩ መልእክት ለኤልሣቤጥ ባለፈ ሠዓት፣ በስተርጅናዋ ለማሀፀኗ ልጅን የሰጠ አንቺንም በድንግልና ሳለሽ ለማህጸንሽ ልጅ ይሰጣል የሚል ነው። የቅ.ኤልሳቤጥ በስተርጅና የድንግል ማርያም በድንግልና የመውለድ ጸጋ የሆነው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና

     ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና:-

የመልአኩ ማሳረጊያ ቃል፣ ማሸነፊያ ብርታት የሆነው ይህ ቃል ነው። ሰው የሚቻለውን ይችላል። አግዚአብሔር የማይቻለውን ይችላል። ሰው እግዚአብሔር አሰችሎት ይችላል። እግዚአብሔር ግን ማንም ሳያስችለው ይችላል!
ማርያምም እነሆኝ የጌታ ባርያ እንደቃልህ ይሁንልኝ
የጌታ ባርያ ነኝ የሚል ፈቃዱን በእግዚአብሔር ፈቃድ የሚለውጥ ነው። እንደቃሌ ሳይሆን እንደቃልህ፣ እንደወሰድሁት ሳይሆን እንደሰጠኸኝ፣ እንደአሳቤ ሳይሆን እንደ ፈቃደህ፣ እኔ ላድርግ ሳይሆን ይሁንልኝ፣ እንደመሰለኝ ሳይሆን እንደወሰንከው፣ ስማኝ ሳይሆን ልስማህን የሚያስቀድም ነው!
                                                                                                                          ወስብሐት ለእግዚአብሔር

FeedBurner FeedCount