Monday, March 3, 2014

ቅድስት ዘሠሉስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ

ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

 ከልዑላን በላይ ልዑል፣ ከቅዱሳን በላይ ቅዱስ፣ የእርሱን ቅድስና ሌሎች ሲጠሩበት የእርሱ የማይከፈልበት፣ በአንድነት የሚመሰገን፣ በሦስትነት የሚቀደስ፤ ሠላምን በሞቱ፣ የገዛ ህይወትን በደሙ የመሰረተ፤ ቤቱን በማይፈርስ የሃይማኖት ምስክርነት ላይ ያነጸ፣ ቅዱሳን ተብለን ልንጠራ አባታችን ልንለው ሥልጣንን የሰጠን፣ ጸጋን ለሁሉ እንደችሎታ በሚያድለው አምላክ ስም ሁላችሁ በያላችሁበት ሰላሙ ይደረግላችሁ፡፡

Sunday, March 2, 2014

ቅድስት ዘሠኑይ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 23 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ
ጸልዩ ከምቅድመንባበ ዝንቱ ክርታስ

ይኄይሰኒ ሕገ አፉከ እምአእላፍ ወርቅ ወብሩር ወይጥእም እመዐር ወሶከር - ከብዙ ወርቅና ብር የአፍህ ህግ ይሻለኛል፡፡ እንደ ስኳርና እንደ ማር ይጥማልና፡፡በሚጥም አንደበቱ ጌታ አክብሮ አንደበቱን ያጣፈጠለት ዜመኛ የሰኞ ቅድስት ድርሰቱን ሲጀምር ባዜመበት ቃል ጀምረንንጉሰ ሰላም ሰላመከ ሀበነ - የሰላም ንጉሷ ሰላምህን ስጠንብለን እኛም ከእርሱ ጋር በማዜም በተሰጠን ሰላም ከዛሬ የድርሰቱን አንዳንድ ቃላትን እንላለን፡፡

Saturday, March 1, 2014

ቅድስት (ይህች ዕለት የተቀደሰች ናት)


(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 22 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ

ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ
 ከአንድ ግንድ ላይ በቅለን ከአንዱ ከኢየሱስ ክርስቶስ አካል ሆነን ከአንዱ ከኢየሱስ ማዕድ የምንበላ የአንዱ አባት ልጆች የሆንን እንደ ብሉይ ሳይሆን በእርሱ ስም ተሰይመን በእርሱ ክርሰቲያን የምንባል አንድነታችን በሞት እንኳን የማይፈታ ቤተሰቦቼ ! ዘለዓለማዊ በሆነው በእርሱ ሰላምታ ደስታ ይሁንላችሁ እላላሁ ። ይህ የሚገባ ነውና ደስ ያላችሁ ደስ ይበላችሁ ብዬ ሰላምታዬን ወደ እናንተ ላክሁ።

Thursday, February 27, 2014

ዘወረደ ዘቀዳሚት ሰንበት



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 21 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ
ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

 እግዚአብሔር ሙላቱ ሁሉ በእርሱ እንዲኖር በእርሱም በኩል በመስቀሉ ደም ሰላምን አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዷልና፡፡ቆላ 1÷19-20 ይህ የመስቀሉ ደም ለደማውያኑም ለመንፈሣውያንም ፍጥረት ፍጹምና ዘለዓለማዊ ሰላምን ሰጥቷል፡፡ ታዲያ እኔም በማትከፈል ሦስትነት በአንድ ሕልውና በምትሆን በእግዚአብሔር ሰላምታ ዘለዓለማዊው ሰላም ይደረግልን ብዬ የአባቴን የቅዱስ ያሬድን የቀዳሚት ሰንበት ዘወረደ ጾመ ድጓ በጥቂቱ የተመረጡ ቃላት እነሆ፡፡

FeedBurner FeedCount