Thursday, March 6, 2014

ቅድስት ዘዐርብ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 27 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ

ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

 በመስቀሉ ፍቅር ተስባችሁ፣ በሞተ ወልዱ ተቀድሳችሁ፣ በጎኑ ውሃ ፍሳሽነት ታጥባችሁ፣ ለእርሱ የተሰጣችሁ የቅዱሳን ወዳጆች የእናታችሁ ልጆች ሰላምና ፍቅር እናንተን ይክበባችሁ በማለትእለቱን ድርሰት ከአባታችን ጋር እነሆ፡፡

Wednesday, March 5, 2014

ቅድስት ዘሐሙስ


በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 26 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ

ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

 ምህረቱን በማንለካው የልብ ጥልቁን በሚያውቀው በብላቴና ድንግል ማህፀን ባደረው የፀሐይ ብርሃን በእርሱ ፊት ጨለማ በሆነ ሰሜንና ደቡብ ምስራቅና ምዕራብ መስዕ እና አዜብ ሳይታወቅ አስቀድሞ በነበረ የፀሐይና የጨረቃን ክበብ እንደ መስታወት በወሰነ ለብርሃናት ጌታቸው በሚሆን በቤተ መቅደሱ በመገናኛው ድንኳን በጥምቀቱ የተወለዳችሁ ሁሉ ከዓለም በሚለየው የጌታ ሰላም ለእናንተ ሰላም ይሁን፡፡ ከኮከብ ለምትበራ፣ ከተራሮች ሁሉ ከፍ ከፍ ላለችው፣ ብርሃኗ የእውነት ፀሐይ ለሆነው ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሚያቀርበው ውዳሴ እና የፆምን ነገር ከሊቁ ጋር እያወደስን እየተማርን እንቆያለን፡፡

Tuesday, March 4, 2014

ቅድስት ዘረቡዕ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 25 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ
ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ
 ‹‹ ሐዋዘ ብርሃነ እግዚኦ ነግሐ ነቂሐነ እምንዋም ንጊሣ ለቤተክርስቲያን ኃበ የኃድር ብዕለ ስብሐቲሑ ንስአል እም ሐቤሁ ረድኤተ ወሕይወተ ኩሉ ዘጌሰ ወመጽአ ኢይጻሙ - አቤቱ ያማረ ብርሐንን ስጠን፤ ነጋ ከእንቅልፋችንም ነቃን፤ የምስጋናው ሐብት ወደሚያድርባት ወደ ቤተ-ክርስቲያን እንገስግስ፤ የሁሉ ህይወት ከሚሆን ከእርሱም እርዳታን እንለምን፤ ወደ እርሷ የገሰገሰ የመጣም አይደክምም፡፡›› ቀኑን ሰላም አውሎ ሌሊቱን ሰላም አሳድሮ ትናንት የነበሩት በሌሉባት ዛሬ ነገን ተስፋ እናደርግ ዘንድ ጠብቆ ለዚህ ያደረሰንን አምላካችንን አመስግነን ቅዱስ ያሬድ እንደሚነግረን ስለማይነገር ስጦታው የምንከፍለው የሌለን በቤቱ በመገስገስ ህይወትን ለምነን አመስግነን በደስታ እንኖር ዘንድ አምላኬ እና መድኃኒቴ በሚሆን በክርስቶስ የመድኃኒቴ ዘውድ በሚሆን በአባቱ የቅድስናዬ መገኛ በሚሆን መንፈስ ቅዱስ በከበረች እናቴ የገነት ሙሽራ ድንግል ማርያም እንዲሁም ሰላማቸው በበዛ በማኅበረ ጻድቃን ስም ሁሉ ሰላማችሁ ይብዛ እላለሁ፡፡

FeedBurner FeedCount