Monday, September 22, 2014

ሥነ ፍጥረት (ለሕፃናት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 12 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ልጆች እንደምን ከረማችኁ? የዕረፍት ጊዜአችኁ እንዴት አለፈ? መልካም ልጆች፡፡ እንግዲኽ ዘመነ ማርቆስ አልፎ አኹን ዘመነ ሉቃስ ገብተናል፡፡ ለአዲሱ ዓመት ያደረሰንን አምላክ እያመሰገንን በዚኽ ዓመት ደግሞ ጊዜያችንን በአግባቡ ተጠቅመን፣ በትምህርታችንም በርትተን ለጥሩ ውጤት መብቃት አለብን እሺ፡፡ ምክንያቱም ጊዜውን በአግባቡ የማይጠቀም ልጅ መጨረሻው አያምርም እሺ ልጆች፡፡ ስለዚኽ ጊዜአችንን በአግባቡ መጠቀም አለብን፡፡ ለዚኽም እግዚአብሔር ይርዳን፡፡

Friday, September 19, 2014

"እርግና"



በዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ


(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 9 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

የእድሜ ጅራፍ ግርፋቱ = ከግንባሬ
የክብር ሸማ ሽበቱ = ከጠጉሬ
የአዝማናት ፍኖት ንቃቃት = ተረከዜ
የምድር ሩጫ ሥጦታ = "ደም- ወዜ"
ለቁጥር መሳፍርት = ብልጥግና
ዳግም ለንሰሃ ............ ዳግም ለምስጋና
ጊዜ ለእርጋታ..... ጊዜ ለጥሙና
ፍፃሜ መዋዕል ......... ድህረ ውርዝውና

Monday, September 15, 2014

የትምህርተ ሃይማኖት መግቢያ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 5 ቀን፣ 2007 ..)- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 “ሃይማኖትማለት አምነ፣ አመነ ከሚል የግእዝ ግሥ የወጣ ሲኾን መዝገበ ቃላታዊ ትርጓሜውምማመን፣ መታመንማለት ነው፡፡ በምሥጢራዊው ትርጕሙ ግንሃይማኖትማለት ፍጥረትን ኹሉ ካለ መኖር ወደ መኖር ያመጣ አንድ እግዚአብሔር እንዳለ፣ ለሚታየውም ለማይታየውም ፍጥረት ሠራዒውና መጋቢው ርሱ ብቻ እንደኾነ፣ ልዩ ሦስትነት እንዳለው፣ በዚኽ አለ በዚኽ የለም የማይባል ምሉዕ በኵለሄ እንደኾነ፣ማመን መታመን ማለት ነው፡፡

Tuesday, September 9, 2014

ዘመኔን አድሰው


በወርቅነሽ ቱፋ
ይኸው
ሩቅ ያልኩት ቀረበ፥ ነገ ዛሬ ሊኾን፥ መጣ እየበረረ፤
በለስ ሕይወቴም ሲፈተሸ፥ ምንም አላፈራ፥ አላዘረዘረ፡፡

FeedBurner FeedCount