Saturday, May 19, 2012

የዮሐንስ ወንጌል የ8ኛው ሳምንት ጥናት (ዮሐ.1፡35-42)!!

“በነገው ደግሞ ዮሐንስ ከደቀ መዛሙርቱም ሁለት ቆመው ነበር፥ ኢየሱስን ሲሄድ አይቶት፡- እነሆ የእግዚአብሔር በግ አለ።” /ቁ.35-36/
 የሰው ልጅ በባሕርይው ሐዋርያው፡- “ስለ አንድ ነገር መልሼ ልጽፍላችሁ አይታክተኝም፤ እናንተን ያበረታችኋልና” እንዳለው ተደጋግሞ ካልተነገረው በቀር ተሎ አይገባውም /ፊል.3፡1/፡፡ ለዚህም ነው መጥምቁ ከዚህ በፊት የተናገረውን ቃል መልሶ የሚነግራቸው፡፡ ሲነግራቸውም መንደሩ እየዞረ ሳይሆን ሁሉም ወደ ባሕረ ዮርዳኖስ እንዲመጡ በማድረግ ነበረ፡፡ “ለምን እንዲህ አደረገ?” ብለን ስንጠይቅም አንደኛ ሌሎች እርሱን የሚመስሉ ሐሰተኞች ዮሐንሶች በተነሡ ነበር፤ ሁለተኛ ሕዝቡ ሁሉም በተሰበሰበበት ሁኔታ “እነሆ የነገርኳችሁ በግ” ቢላቸው የበለጠ ታማኝነትን ያገኛል፤ ሦስተኛ ምስክነቱ እውነት እንደሆነ (ከዝምድናው የተነሣ እንዳልሆነ) አብም መንፈስ ቅዱስም ሲያረጋግጡት ሕዝቡ የበለጠ ያምናል፤ አራተኛ አይሁድ ክርስቶስ ሕግ አፍራሽ ነው ብለው ላለማመናቸው ምክንያት እንዲያጡ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ነበረበት፡፡ ነብያትን መታዘዝ ጽድቅ ነውና፡፡ ስለዚህ ሚዜው ሙሽራይቱን ከሙሽራው ጋር ለማገናኘት አሁንም ከወንዙ ዳር ቆሞ “እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ በግ” እያለ ይጮኽ ነበር /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ የዮሐ. ወንጌል ትርጓሜ ድርሳን 18፣ ድርሳን በእንተ ጥምቀት/፡፡
  ከዚህ በኋላ ሁሉም ሳይሆኑ “ሁለቱም ደቀ መዛሙርት ዮሐንስ ይህን ሲናገር ሰምተው ኢየሱስን ተከተሉት።” /ቁ.37/ እውነት ነው! ፀሐይ ከወጣች በኋላስ የሻማ ጥቅሙ ምንድነው? የዮሐንስ ጥምቀትስ የክርስቶስ ጥምቀት ከመጣች በኋላ ምን ረብሕ አላት? /ቅ.ኤፍሬም ሶርያዊ Commentary on Tatians Diatessaron 4:17/፡፡
ክርስቶስም ሲከተሉት አይቶ በልባቸው ምን እንደሚፈልጉ ስለማያውቅ ሳይሆን ፈቃደኝነታቸውን ለመጠየቅ “ምን ትሻላችሁ?” አላቸው /ቁ.38/፡፡   እነርሱም “ረቢ፥ ወዴት ትኖራለህ?”  በማለት የሚፈልጉት እንዲያስተምራቸው እንደሆነና ወዴት እንደሚኖር በግልጽ ነገሩት፡፡ እርሱም “መጥታችሁ እዩ” አላቸው። መጥተውም ለቀበሮዎች ጕድጓድ ለሰማይም ወፎች ማረፍያ ጐጆ እንዳላቸው ክርስቶስ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት እንደ ሌለው አዩ፤ በዚያም ቀን እስከ አሥር ሰዓት ድረስ በእርሱ ዘንድ ሲማሩ ዋሉ /ቁ.39፣ ሉቃ.9፡58/፡፡ እስራኤል ዘሥጋ ሆነው ሄደውም እስራኤል ዘነፍስ ተባሉ /ቴዎዶር ዘሜውፕሳስትያ Commentary on John 1:1:38/፡፡
 “ከዮሐንስ ዘንድ ሰምተው ከተከተሉት ከሁለቱ አንዱ የስምዖን ጴጥሮስ ወንድም እንድርያስ ነበረ” /ቁ.40/፡፡ ምንም እንኳን ስሙ የተጠቀሰው እንድርያስ ብቻ ቢሆንም ሁለተኛው ግን ወንጌላዊው ዮሐንስ ራሱ ነበር፡፡ “እንዴት ይታወቃል?” ቢሉ ወንጌሉን ሲጽፍ የተለያየ ቦታ ስለ እርሱ የሚነገሩትን “ጌታ ይወደው የነበረ ደቀ መዝሙር” ይላል እንጂ በሙሉ ስለ ትሕትና ብሎ ስሙን አይጠቅስምና /ዮሐ.19፡26፣ ቴዎዶር ዘሜውፕሳስትያ ዝኒ ከማሁ/፡፡
“እንድርያስም አስቀድሞ የራሱን ወንድም ስምዖንን አገኘውና፡- መሢሕን አግኝተናል አለው፤ ትርጓሜውም ክርስቶስ ማለት ነው። ወደ ኢየሱስም አመጣው” /ቁ.41/፡፡ የሚገርም ነበር! ሰብአ ሰገል “የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው?” ብለው ጠይቀው ለራሳቸው አግኝተውት ስለሄዱ አሁን እንድርያስ ሲያገኘው በጣም ነበር የተደሰተው፡፡ ምክንያቱም መጥምቁ የሚጠበቀው መሲሕ እርሱ መሆኑን ነግሮዋቸዋል፤ መንፈስ ቅዱስ ሲመሰክር አይተዋል፡፡ ክርስቶስም እርሱ ማን እንደሆነ ነግሮታል፡፡ እንድርያስ ያልተማሩና የተናቁ የገሊላ ሰዎች በመሆናቸው መሲሑን ሲያገኘው በጣም ተደስቷል፡፡ “በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃን ወጣለት” የሚለው የነብዩ ቃል ሲፈጸምለት በዓይኑ አይቷል /ኢሳ.9፡1/፤ “ምናምንቴዎችን መረጠ” የሚለው ቃል ሲፈጸምለት የማይደሰትስ ማን ነው? /1ቆሮ.1፡27፣ ኤፍሬም ሶርያዊ ዝኒ ከማሁ/፡፡ የሚደንቀው ደግሞ እንድርያስ እዚያ ተቀምጦ አልቀረም፤ ወንድሙን ይጠራ ዘንድ ተፋጠነ እንጂ፡፡ በሰዓታት ጊዜ ውስጥ ተምሮና አምኖ “መሲሕን አግኝተናል” እያለ ወንድሙን ለመስበክ ተቻኮለ፡፡ በጣም በጉጉት ሲጠብቀው እንደነበረም ያመለክታል /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 19/፡፡
 “ኢየሱስም ስምዖንን ተመልክቶ። አንተ የዮና ልጅ ስምዖን ነህ፤ አንተ ኬፋ ትባላለህ አለው፤ ትርጓሜው ጴጥሮስ ማለት ነው” /ቁ.42/፡፡ ጴጥሮስ ለመጀመርያ ጊዜ ስሙ የሚቀየረው በዚሁ ሰዓት ነው፡፡ ጴጥሮስ ማለት ዐለት ማለት ነው፡፡ ይህም የቤተ ክርስቲያን መሠረት ጽኑ እና የማይነዋወጥ መሆኑን ያመለክታል /ማቴ.7፡24፣ ማቴ.16፡18፣ አውግስጢኖስ ዝኒ ከማሁ 7፡14/፡፡
 “ክርስቶስ ለአንዳንዶቹ ሐዋርያት ስማቸውን የሚቀይርላቸው ለምንድነው?” ብለን ስንጠይቅም በብሉይ ኪዳንም አብራምን አብራሃም፣ ሦራን ሣራ፣ ያዕቆብን እስራኤል ያለ አምላክ እርሱ እንደሆነ እንገነዘብ ዘንድ ነው /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒ ከማሁ/፡፡
 ሳንወደው ለወደደን ከዲያብሎስ መንጋጋ አላቅቆም ወዳጆቹን ላደረገን ለእግዚአብሔር ዛሬም ዘወትርም ስሙ የተመሰገነ ይሁን አሜን!!

የእግዚአብሔር በግ (የዮሐንስ ወንጌል የ7ኛው ሳምንት ጥናት)!!

“በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ። እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።” ዮሐ.1፡29
 የሚገርም ምስክርነት ነው፡፡ ጌታስ “በሰው ፊት የሚያምንብኝን ሁሉ እኔም በእግዚአብሔር መላእክት ፊት አምነዋለሁ” አይደል ያለው /ሉቃ.12፡8/፡፡ መጥምቁ ምስክርነቱን ለአይሁድ ሁሉ ላንቃው እስኪሰነጠቅ ድረስ “ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ዘያአትት ወያሴስል ኃጢአተ ዓለም- የሰውን ኃጢአት የሚያስተሰርይ የእግዚአብሔር መሥዋዕቱ እነሆ!” ይላቸው ነበር /John Chrysostom, Homily on the Gospel of John, 17/፡፡ አዎ! ዮሐንስ ከእንግዲህ ወዲህ ዝግጅቱን ጨርሷል፡፡ ያ ለስድስት ወራት ሲያዘጋጀው የነበረና ለዓለም ሁሉ የሚሠዋው ንጹሑ በግ መጥቷልና /2ቆሮ.5፡14፣ ቅ.ቄርሎስ ዘአሌክሳንድርያ Commentary on the Gospel of John 2:1/፡፡ ይህ ንጹሕ በግ እንደ ብሉይ ኪዳኑ ዓይነት በግ አይደለም፤ ይህ በግ ነብዩ “እኔም ለመታረድ እንደሚነዳ እንደ የዋህ በግ ጠቦት ሆንሁ” ያለው ነው /ኤር.11፡29፣ አርጌንስ Commentary on the Gospel of John 6/፡፡ ይህ በግ ኢሳይያስ “በሸላቾቹ ፊት ዝም አለ” ያለለት በግ ነው /ኢሳ.53፡7፣ አውሳብዮስ ዘቂሳርያ Proof of the Gospels 1:10/፡፡ ይህ በግ በዕጸ ሳቤቅ (በእመቤታችን) ተይዞ የተገኘውና በይስሐቅ ፈንታ የተሠዋው በግ ነው /ዘፍ.22፡13፣ አውግስጢኖስ Sermon 19:3/፡፡ ይህ በግ በምድረ ግብጽ ሞተ በኩር በመጣ ጊዜ በእስራኤላውያን በኩራት ፈንታ የተሠዋው በግ ነው /ዘጸ.12፡21-30/፤ ይህ በግ አቤል ለእግዚአብሔር ያቀረበው ንጹሑ በግ ነው /ዘፍ.4፡4፣ አምብሮስ/፡፡
 መጥምቁ በዚያ ለነበሩ አይሁድ ይህን ሁሉ የሚመሰክርላቸው በመጻሕፍቶቻቸው የተነገረውን ትንቢት ሁሉ መፈጸሙን አውቀው በክርስቶስ እንዲያምኑ ነው /ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒ ከማሁ/፡፡
 የሚደንቅ ነው! ይስሐቅ ከርብቃ ጋር /ዘፍ.24/፣ ያዕቆብ ከራሄል ጋር /ዘፍ.29/፣ ሙሴም ከሲፓራ ጋር ለመጋባት በውኃ ጉድጓድ እንደተገናኙ ሁሉ /ዘጸ.2፡15-21/ ክርስቶስም ከሙሽራው ከቤተ ክርስቲያን ጋር በዮርዳኖስ ወንዝ ተጋብቷል /ኤፌ.5፡32፣ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ Commentary on Tatians Diatessaron 3:17/፡፡
 መጥምቁ ምስክርነቱን ይቀጥልና “አንድ ሰው ከእኔ በኋላ ይመጣል፥ ከእኔም በፊት ነበርና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል ብዬ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነው።” ይላቸዋል /ቁ.30/፡፡ እንዲህ ማለቱ ነበር፡- “የዓለምን ኃጢአት ያስወግዳል ያልኳችሁ በግ፣ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል ያልኳችሁ ሰው እርሱ ነው፡፡ እርሱ አወጣጡ ከዘላለም የሆነ አምላክ ነው፤ እኔ ግን አይደለሁም፡፡” አሁንም ይቀጥልና “እኔም አላውቀውም ነበር” ይላል/ቁ.31/፡፡ “ታድያ ካለወቅከው እንዴት ትመሰክራለህ? ካላችሁኝም ‘አላውቀውም ነበር’ አልኳችሁ እንጂ ‘አላውቀውም’ አላልኩም ብዬ እመልስላችኋለሁ፡፡ ‘አወጣጡ ከዘላለም ከሆነ ታድያ አሁን ካንተ ዘንድ ለመጠመቅ ምን አተጋው?’ ካላችሁኝም እንዲህ እላችኋለሁ ‘ለእስራኤል ይገለጥ ዘንድ ስለዚህ በውኃ እያጠመቅሁ እኔ መጣሁ’ ብዬ እመሰክራችኋለሁ፡፡ እርሱስ እንደ እኔና እንደናንተ ጥምቀት የሚያስፈልገው አይደለም፡፡ ‘ቅድም አላውቀውም ነበር ብለኸን ነበር፡፡ አሁን እንዴት አወቅከው?’ ካላችሁኝ ‘መንፈስ ከሰማይ እንደ ርግብ ሆኖ ሲወርድ አየሁ፤ በእርሱ ላይም ኖረ። እኔም አላውቀውም ነበር፥ ዳሩ ግን በውኃ አጠምቅ ዘንድ የላከኝ እርሱ፡- መንፈስ ሲወርድበትና ሲኖርበት የምታየው፥ በመንፈስ ቅዱስ የሚያጠምቅ እርሱ ነው አለኝ’ እላችኋለሁ” /ቁ.32-33/፡፡  መጥምቁ እየደጋገመ “አላውቀውም ነበር” የሚለን ስለ ክርስቶስ የሚሰብከው ሁሉ “ተዛምዶተ ሥጋ ኑሮት ነው፤ ማማለጃ ተቀብሎ ነው፤ አብሮ አደግ ሁኖ ነው” ብሎ ማንም እንዳያስብ ነው፡፡ በበረሀ የማደጉ አንዱ ምሥጢርም ይኸው ነበር /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒ ከማሁ/፡፡
 የመንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል መውረድ ሌላ የሚያስገነዝበን ምሥጢር አለው፡፡ ይኸውም እንዲህ ነው፡- መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን ሰው በእግዚአብሔር መልክ እና ምሳሌ  ተፈጥሯል፡፡ እግዚአብሔር ሰውን ከአፈር ካበጃጀው በኋላ እፍ ሲልበት መልኩን ሥሎበታል፡፡ ሲበድል ግን ይህ መልኩ ተበላሽቷል፤ የጸጋ ልብሱ ቆሽሾአል፡፡ የተሰጠው መንፈስ ቅዱስ እየራቀው ሄደ፡፡ ፈጣሪውንም እየረሳ ሄደ፡፡ መፍቀሬ ሰብእ እግዚአብሔር ግን የተበተነውን መንጋ መሰብሰብ ወደደ፡፡ የሰው ልጅ በመጀመርያው አዳም ያጣውን ጽድቅም በሁለተኛው አዳም መታዘዝ የእግዚአብሔር ቤተ ሰብእ አደረገው /2ቆሮ.5፡21/፡፡ መንፈስን የሚያድል ክርስቶስም ከእኛ ርቆ የነበረውን ቅዱስ መንፈስ በእኛ ተገብቶ ተቀበለው፡፡ በኃጢአታችን ምክንያት የራቀው መንፈስ ቅዱስ በክርስቶስ ንጽሕና ወደ እኛ ተመለሰ /ቅ.ቄርሎስ ዘአሌክሳንድርያ፣ ዝኒ ከማሁ/፡፡ በኖኅ ጊዜ እንደተደረገውም ያ መንፈስ ቅዱስ ለቤተ ክርስቲያን ሰላም ሲያውጅ ተመልክተናል /ቅ.ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም፣ Catechetical Lecture 17:9/፡፡
 ከእናንተ መካከል “አይሁድ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ሲወርድ እየተመለከቱ እንዴት በክርስቶስ አላመኑም?” ብሎ የሚጠይቅ ሊኖር ይችላል፡፡ እኔም እንዲህ ብዬ እመልስለታለሁ፡- “ነገረ እግዚአብሔር በዓይነ ሥጋ ብቻ በማየት አይገባም፤ ይልቁንም በዓይነ ልቡና አይቶ ማስተዋልን ይጠይቃል እንጂ” /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒ ከማሁ/፡፡
መጥምቁ ንግግሩን እንዲህ ብሎ ይጨርሳል፡- “እኔም አይቻለሁ-  ከመ ዝንቱ ውእቱ ወልዱ ለእግዚአብሔር- እርሱ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ እንደ ሆነ መስክሬአለሁ” /ቁ.34/፡፡
እውነት ነው!! ሁላችንም ክርስቶስ እርሱ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ እንደሆነ፤ በአንድነት በሦስትነት የሚመሰገን አምላክ እንደሆነ፤ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዳለው፤ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቁጣ በእርሱ ላይ እንደሆነች ልንመሰክር ያስፈልጋል፡፡ ይህን ሁሉ በአፍም በመጣፍም እንዲሁም በምግባር እንገልጠው ዘንድ ሰውን በመውደድ ሰው የሆነው ክርስቶስ ይርዳን አሜን!!!

የዮሐንስ መጥምቅ ምስክርነት (የዮሐንስ ወንጌል የስድስተኛው ሳምንት ጥናት)!!

“አይሁድም አንተ ማን ነህ? ብለው ይጠይቁት ዘንድ ከኢየሩሳሌም ካህናትንና ሌዋውያንን በላኩበት ጊዜ፥ የዮሐንስ ምስክርነት ይህ ነው” /ቁ.19/፡፡  ቅናት ክፉ ነገር ነው፡፡ ክፋትነቱም ለአድራጊው እንጂ ለሚደረግበት ሰው አይደለም፡፡ ሐዋርያውስ፡-“ብትበደሉ አይሻልምን? ብትታለሉስ አይሻልምን?” አይደል ያለው /1ቆሮ.6፡7/? ወንጌላዊው እነዚህ አይሁድ ከየት እንደመጡ የሚነግረን ያለምክንያት አይደለም፡፡ ከዋናው ቤተ መቅደስ የመጡ እጅግ ክፉዎች መሆናቸውን ለመናገር እንጂ፡፡ ዮሐንስ ማን መሆኑን እማ “ይህ ሕጻን ምን ይሆን” እያሉ ሲደነቁ ነበርና /ሉቃ.1፡66፣ St. John Chrysostom homily on the Gospel of John, homily 16/፡፡ ተራው ሕዝብ ግን መጥምቁ በሚናገረው ሁሉ በጣም ስለሚማረኩ በቀላሉ የሚለውን ሁሉ ያምኑት ነበር፡፡ ስለዚህም ራሱን ከፍ ከፍ ለማድረግ ዕድል ነበረው፤ “አዎ መሲሑ ነኝ” ቢላቸው እንኳን ባላንገራገሩ ነበር፤ አላደረገውም እንጂ /Augustin sermon 289:4/፡፡ ካህናቱና ሌዋውያኑ ግን አይቀበሉትም፡፡ በእውነትም የእፉኝት ልጆች ናቸው፡፡ ወደ ወንዙ እየመጡ ሲጠመቁ የነበሩ ሰዎች አሁን ከሕዝቡ የሚቀበሉትን ከበሬታ ስለቀነሰባቸው “ማን ነህ” ይሉት ጀመር፡፡ ብጹዕ ዮሐንስ ግን ተራው ሕዝብ “መሲሑ ሊሆን ይችላል” የሚለውን የተሳሳተ ግንዛቤአቸው ለማቅናት ሳይክድ “እኔ ክርስቶስ አይደለሁም” ይላቸው ነበር፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን የእነዚህ ክፉ እረኞች ምክንያታዊነትም ከንቱ ለማድረግ ወንጌላዊው “ዮሐንስ መሰከረ” እያለ ሦስት ጊዜ ይነግረናል /ቁ.8፣ 15፣ 20/፡፡
 ከዚያ በኋላ ወደ ሌላ ጥያቄ ያመሩና፡- “እንኪያስ ማን ነህ? ኤልያስ ነህን?” ይሉታል /ቁ.20/፡፡ ምክንያቱም ከመሲሑ በመቀጠል በጉጉት የሚጠብቁት ኤልያስ ነው፡፡ ነገር ግን ምንም እንኳን ኤልያስ የዳግም ምጽዓት አዋጅ ነጋሪ በመሆን ከዮሐንስ ጋር ቢመሳሰልም “እኔ ኤልያስ አይደለሁም” ይላቸው ነበር /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒከማሁ/፡፡
 ምናልባት ከእናንተ መካከል ጌታ፡- “`ኤልያስስ መጥቷል` ካለው ጋር አይጋጭምን?” ብሎ የሚጠይቅ ሰው ሊኖር ይችላል /ማቴ.17፡10/፡፡ በፍጹም! ምክንያቱም ቅዱስ ገብርኤል ይህንን ሐሳብ ግልጽ ሲያደርግልን “እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ… በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል” ብሎናል /ሉቃ.1፡17/፡፡ ይህም ማለት “ዮሐንስ በኤልያስ መንፈስ መጣ እንጂ በቁሙ ኤልያስ አይደለም” ማለት ነው፡፡ እውነት ነው! ኤልያስ የዳግም ምጽዓት አዋጅ ነጋሪ እንደሆነ ሁሉ በኤልያስ መንፈስ የመጣው ዮሐንስም ለመጀመርያው ምጽዓት አዋጅ ነጋሪ ነበርና /Gregory the Great, Forty Homelies, 4/፡፡
  አሁንም ይቀጥሉና፡- “ታድያ ኤልያስ ካልሆንክ በኦሪት ዘዳግም ሙሴ ይመጣል ያለው ነብዩ ነህን?” ብለው ለሦስተኛ ጊዜ ይጠቁታል /ዘዳ.18፡15፣ Origen: commentary on the Gospel of John/፡፡ እርሱ ግን “ነብይ አይደለሁም” ሳይሆን “እናንተ የምትሉት ነብይ አይደለሁም” ይላቸው ነበር /ማቴ.11፡9፣ ታላቁ ጐርጐርዮስ ዝኒ ከማሁ/፡፡
 የሚገርመው ግን እነርሱም ጥያቂያቸውን ሳይሰለቹ ይጠይቁታል እርሱም ሳይሰለች ይመልስላቸዋል /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒ ከማሁ/፡፡ “እንኪያስ ማን ነህ? ለላኩን መልስ እንድንሰጥ፤ ስለራስህ ምን ትላለህ? አሉት” /ቁ.22/፡፡ እርሱም በሕዝቡ ልቡና ያለውን የተሳሳተ ግንዛቤና በእነዚያ ያለውን ተንኰል ከንቱ ካደረገ በኋላ እነርሱ ከሚቀበሉት መጽሐፍ እየጠቀሰ፡- “እኔ በበረሀ የሚጮህ ድምጽ ነኝ፤ ከእኔ በፊት የነበረውና አሁን ሥጋ ለብሶ በመካከላችሁ የቆመው ቃል ግን የምትጠብቁት መሲሕ ነው” እያለ የነቢዩ ኢሳይያስን የትንቢት ፍጻሜ ይነግራቸው ነበር /ቁ.23፣ ኢሳ.40፡3፣ ታላቁ ጐርጐርዮስ ዝኒ ከማሁ 6/፡፡ እንዲህ እያደረገም ልቡናቸውን የንስሐ ፍሬ አፍርቶ ለጌታ እንዲያዘጋጁ አጥብቆ ያስተምራቸው ነበር፤ ሁሉም እንዲሰሙትም ጮክ ብሎ ይናገር ነበር፤ ከእግዚአብሔር ጸጋ ተራቁታ የነበረችው ነፍስ ከአምላኳ ጋር እንድትገናኝ ያዘጋጅ ነበር /አርጌንስ ዝኒ ከማሁ 6፡100/፡፡
 “የተላኩትም ከፈሪሳውያን ነበሩና። እንኪያስ አንተ ክርስቶስ ወይም ኤልያስ ወይም ነቢዩ ካይደለህ፥ ስለ ምን ታጠምቃለህ? ብለው ጠየቁት” /ቁ.24/፡፡ አስቀድመን ቅናት ያልነው እንግዲህ ይኸው ነው፡፡ ምክንያቱም መጥምቁ ማንነቱን በትክክል እየነገራቸው እንኳን ይሰናከሉበት ነበርና /ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒከማሁ/፡፡ ዮሐንስ ግን የእርሱ ጥምቀት በኢየሱስ ክርስቶስ ለምትመጣው ፍጽምት ጥምቀት የማዘጋጀት አገልግሎት እንደሆነች “እኔ በውኃ የንስሐ ጥምቀት አጠምቃለሁ፤ ዳሩ ግን እናንተ የማታውቁት ልጅነትን በምታሰጥ ጥምቀትም የሚያጠምቅ በመካከላችሁ ቆሞአል” እያለ ይነግራቸው ነበር /St. Cyril of Alexandria Commentary on the Gospel of John 1:10/፡፡ በእርግጥም የዮሐንስ ጥምቀት ለንስሐ የምታዘጋጅ እንጂ መንፈስ ቅዱስን የምታሰጥ አልነበረችም /ታላቁ ጐርጐርዮስ ዝኒከማሁ 4 /፡፡
 እነዚህ ክፉዎች ይዘውት ለመጡት ተንኰልና በሕዝቡ ልብ የነበረውን የተሳሳተ ግንዛቤ በመቃወምና በጣቱ እያመለከተ፡- “እነሆ እናንተ በመለኰቱ አይታችሁት የማታውቁ አሁን ሥጋ ለብሶ በእናንተ መካከል አለ፤ እርሱ በመጀመርያ ቃል የነበረ ነው፤ አሁን ግን በምልዓት ያልተለየውን ዓለም ሥጋ ለብሶ ጎብኝቶታል፤ እርሱ ከእኔ ይበልጣል፤ እኔ ግን የጫማውን ጠፍር እንኳን መፍታት የማይገባኝ ወራዳ ነኝ፤ ዮሐንስ ይበልጣል የሚለው የተሳሳተ ግንዛብያችሁ አስወግዱና ከእኔ ይልቅ ወደ እርሱ ዘወር በሉ፤ እኔ ሚዜ ነኝ እርሱ ግን ሙሽራ ነው” እያለ ለሁሉም ይመልስላቸው ነበር /Apolinaris of Laodicea, Fragments on John 5/፡፡ በጥንት ጊዜ፥ ማንም ቢሸጥ ቢለውጥም፥ ነገሩን ለማጽናት ሰው ጫማውን እንዲያወልቅ ለባልንጀራውም እንዲሰጠው በእስራኤል ዘንድ ልማድ ነበረ /ሩት.4፡7/፡፡ ሙሽራይቱ (ቤተ ክርስቲያን) ያለችው ደግሞ እርሱ ክርስቶስ እንጂ ዮሐንስ አይደለም፡፡ ስለዚህ መጥምቁ “እንኳንስ ሙሽራ ልሆን ቀርቶ እርሱ የረገጣትን ኮቴ እንኳን ልረግጥ አይገባኝም” ማለቱ ተገቢ ነበር /ታላቁ ጐርጐርዮስ ዝኒከማሁ 4/፡፡
 ይህ ሁሉ በሰዋራ ቦታ ሳይሆን ሕዝቡ በተሰበሰበበት ዮሐንስም ያጠምቅበት በነበረው በዮርዳኖስ ማዶ በቢታንያ እና በቤተ ራባ ሆነ /ቁ.28፣ ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ዝኒ ከማሁ/፡፡
 ወንድሞቼ! ሴቶች ከወለዷቸው ሁሉ ከእርሱ የሚበልጥ የሌለ ዮሐንስ የጌታን የጫማ ማዘብያ መንካት አይገባኝም ካለ እኛማ ምን ያህል ያልተገባን እንሆን ይሆን? ዓለም ለእርሱ ያልተገባችው ይልቁንም ዕድሜውም በሙሉ እግዚአብሔርን በማገልገል አንገቱ የተሰየፈው ዮሐንስ እንዲህ ካለ በኃጢአት የጨቀየን እኛማ ምን እንል ይሆን? ትሕትናው እንዴት ከፍ ከፍ እንዳደረገችው ታስተውሉ ዘንድ እማልዳችኋለሁ! እርሱ የጫማውን ማዘብያ እንኳን “አልነካም” ቢልም ሰውን አፍቃሪ ጌታ ግን “እንኳንስ ጫማዬ ገና እኔን ታጠምቀኛለህ” ብሎታል፤ “አጥምቆታልም”፤ ጴጥሮስም “ጌታ ሆይ እኔ ኃጢአተኛ ነኝና ከእኔ ራቅ” ቢለውም ሰው ወዳጁ ጌታ ግን “ገና ቤተ ክርስቲያኔን በአንተ ላይ እመሠርታታለሁ” ብሎታል፡፡ እውነት ነው! ትዕቢት ቅዱሳን መላእክትን ርኩሳን መላእክትን ታደርጋለች፤ ትሕትና ግን ወደ ሕይወት ዛፍ የምታስወጣ መሰላል ነች፡፡ ምንም ያህል ጾመኞች፣ ጸሎትን የምናዘወትር፣ ሌላም ሁሉ ብናደርግ ትሕትና ግን ከሌለን የትሕትና ጌታ ከእኛ ጋር የለም፡፡ በሰው ዘንድ ከፍ ከፍ ያለ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን የረከሰ ነውና /ሉቃ.16፡15/፡፡ አቤቱ እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደ በደላችን አይሁን፡፡ አሜን!!  

Friday, May 18, 2012

THE MOST VERSATILE ETHIOPIAN SCHOLAR & SAINT- St. YARED=+=



IN THE NAME OF THE FATHER, THE SON, AND OF THE HOLY SPIRIT ONE GOD AMEN!

Selam=+= (To mean Peace be to you in Ethiopic!)

Here is the second part of what I have promised you in the last time.
St. Yared; the great Ethiopian scholar, was born in Axum (One of the Ancient Cities in the world in Northern Part of Ethiopia and where the Arc of the Covenant lies) in 505 AD (This is Ethiopic calendar. I will present in the future). His father was called Isaac and his mother Christina.

His father died when he was 7. His mother then gave to the then Scholar and his uncle; Gedewon, in the courtyard of Axum Zion church to adopt her son and to take over the responsibility regarding his education. But; St. Yared was not intelligent enough in the beginning to compete with the other children, and His uncle was so impatient with him and he gave him several lashes for his inability not to compete with his peers.
Realizing that he was not going to be successful with his education, Yared left school and went to Medebay, a town where his another uncle resided. On his way to Medebay, not far from Aksum, he was forced to seek shelter under a tree from a heavy rain, in a place called Maikrah. While he was standing by leaning to the tree, he was immersed in thoughts about his poor performance in his education and his inability to compete with his peers. Suddenly, he noticed an ant, which tried to climb the tree with a load of a seed. The ant carrying a piece of food item made six attempts to climb the tree without success. However, at the seventh trial, the ant was able to successfully climb the tree and unloaded the food item at its destination. Yared watched the whole incident very closely and attentively; he was touched by the determined acts of the ant. He then thought about the accomplishment of this little creature and then pondered why he lacked patience to succeed in his own schooling.

He got a valuable lesson from the ant. In fact, he cried hard and then underwent self-criticism. The ant became his source of inspiration and he decided to return back to school. He realized the advice he received from his uncle was a useful advice to guide him in life. He begged Aba Gedeon to forgive him for his past carelessness. He also asked him to give him one more chance. He wants all the lessons and he is ready to learn.

His teacher, Aba Gedewon then began to teach him the Book of David. Yared not only was taking the lessons, but every day he would stop at Aksum Zion church to pray and to beg his God to show him the light. His prayer was answered and he turned out to be a good student. Within a short period of time, he showed a remarkable progress and his friends noticed the change in him. They were impressed and started to admire him. He completed the Old and New Testaments lessons at a much faster pace. He also finished the rest of lessons ahead of schedule and graduated to become a Deacon. He was fluent in Hebrew and Greek, apart from Ge’ez. After that he become a Deacon & served at Axum Zion Church where he late on become a married priest who succeeded to the position of his uncle. He was the first Ethiopian Scholar to compose a hymn. But his hymn was not a result of learning only; but a matter of inspiration. As a matter of inspiration, he was made to enjoy the company of, and listening to the singing of angels (which revealed themselves in the form of three birds!) and then he was taken up in spirit to the heavenly Jerusalem where he could learn the song of the Twenty Four Priests to heaven. When he returned to himself, he went into the church of Axum at the 3rd hour of the day & he began to cry out with a loud voice saying “hale luya laab, hale luya lewold, hale luya wolemenfes qidus qidameha letsion semaye sarere wedagem arayo lemusse zekeme yegeber gibra ledebtera which is to mean Hallelujah to the Father, Hallelujah to the Son, Hallelujah to the Holy Spirit.’’ This was later labeled Mahlete Aryam (The Highest).

His hymn has three modes: Geez, Araray, and Ezil. These three modes are well characterized in a way, which can be used on fast days, ordinary days, and on great festivals.
His literature has unique mystery in his hymnary (In Ethiopic Digwa). He arranged hymns for each season of the year; for summer, winter, spring, and Autumn, and for festivals and Sabbaths, and for the days of St. Mary, Angels, the Prophets, the Martyrs, the Apostles and the Righteous.

St. Yared preached the Gospel throughout Ethiopia. He also composed a song to the Ethiopian Anaphora. There are five hymn books composed by St. Yared. They are: Digwa, Tsome Digwa, Mieraf, Zimare,Mewasiet, and The Chant of the Liturgy.He used to elaborate his hymn in musical notation which in many ways is connected with its religious meaning (symbol). It consists of Biblical signs and letters as well as musical dots placed above the relevant syllables. They indicate the raising or lowering of the voice as well as other modes of pronunciation.

These Signs (Milikt in Ethiopic) serve to instruct the singer in how to instruct the single note and how to interpret the melody (Note that Mozart was not yet born).
The signs are 8. (It is difficult for me to put them here in sign as am not good in drawing! But; you can easily Google it.)

In general the works of Yared would consolidate almost the Theological, Ethical, Musical and Philospphical world of human thought (Qine- to mean Poet in Ethiopic).

St. Yared is the most venerated Holy Father canonized by the church and a great Theologian who could help the Christian Faith to be deeply rooted in the country. The bad news is his writings are not yet translated to other international languages.

The feast of St. Yared is tomorrow, Ginbot 11 E.C. (which is 19th of May in. G.C.).

May the blessings and Intercession of St. Yared be with us and all Christians. Amen!!
(To be continued in other Ethiopic articles)

FeedBurner FeedCount