Showing posts with label ብሒል ወምክረ አበው. Show all posts
Showing posts with label ብሒል ወምክረ አበው. Show all posts

Monday, May 14, 2012

ብሒል ወምክረ አበው- ቁጥር ሁለት!!


©        “ወንጌል ነፍሰ ጡር ነች፤ መምህራንም ያዋልዷታል፡፡”
©       “ተዋሕዶ መናፍቃን የወገባቸውን ጥይት የሚጨርሱባት ሃይማኖት ነች፡፡”
©       “በእግዚአብሔር ዘንድ የሽንት ምርመራ የለም፡፡ ሲፈውስም ተረፈ ደዌ የለውም፡፡”
©       “ሰው ማለት ትልቅ ኢንዱስትሪ ነው፡፡ የሚበላውም ሁሉ ጥሬ ዕቃ ነው፡፡”
©       “አፍህና ልብህ እኩል መሥራት አለባቸው፡፡”
©       “ኦሪት እንደ እስላም የመሸኛ ጫፍ ትፈትጋለች፤ ወንጌል ግን የልብን ሳንኮፋ ትቆርጣለች፡፡”
   (መምህር ደጉዓለም ካሣ)!
v  የፍልስፍና ጣርያው የዋኅና ጥበበኛ መሆን ነው፡፡
v  ዓለም ማለት ልክ እንደ አምፊቲያትር ነች፡፡ ብዙ ተመልካች በዙርያዋ አለ፡፡ ተዋያናዩም ክርስቲያኑ ነው፡፡ ነገር ግን የሚተውነው ጭምብል አጥልቆ ሳይሆን እውነተኛ ሕይወቱን በማሳየት ነው፡፡
v  ልብህ ማየት መመኘትም ካማረው እግዚአብሔር ቀላል መፍትሔ አስቀምጦልሃል፡፡ ይኸውም ሚስትህን በደምብ አድርገህ ማየትም መመኘትም ትችላለህ፡፡ ይህን የሚከለክል ሕግ የለምና፡፡
v  ግብዞች ምጽዋትን ሲሰጡ ለተራበ ሰው አዝነው ሳይሆን እጀ ሰፊ ናቸው ብሎ አላፊ አግዳሚው እንዲያጨበጭብላቸው ስለሚወዱ ነው፡፡ ከዚህ የበለጠ ወንድምን መጥላት ግን የለም፡፡ ምክንያቱም ወንድማቸው በረሀብ እየተሰቃዬ እነርሱ ስለ ክብራቸው ይጨነቃሉና፡፡ አንተ ግን መንፈሳዊነትህ እያደገ ስትሄድ ከእንዲህ ዓይነቱ ከንቱ ነገር ሽሽ፡፡ የሰጠኸውም ሁሉ ሊቆጠር ከማችል ወለዱ ጋር ከላይ ይጠብቅሀል፡፡ መልሶም ላንተ ይሰጥሃል፡፡
     (ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ)! 

Wednesday, May 2, 2012

ምክረ አበው ቁጥር አንድ



v ከጐደለን ይልቅ ያለን ይበልጣል፡፡
v  ተቀብሎ የማያመሰግን ከቀማኛ ይቆጠራል፡፡
v  ለንስሐ የመደብነው ጊዜ ዓለም የማትፈልገውን የዕድሜያችንን ማለቅያ መሆኑ ያሳዝናል፡፡
v  ነገሥታት በክርስቲያኖች ጸሎት ካልታገዙ ሰይጣን ሲያውካቸው ሕዝቡን ያውካሉ፡፡
v  በጠብ ውስጥ ያለ ረሀብ፣ በድሪቶ ውስጥ ያለ ጥጋብ፣ በጐፈሬ ውስጥ ያለ ጽድቅ አይታወቅም፡፡
v  እንደ ዳዊት ስንዘምር እንደ ሜልኮል የሚያሽሟጥጡ አይጠፉም፡፡
v  ሰይጣን ላያስተኛን ተኙ ይለናል፡፡
v  ማርያም የተመሰገነችው በማርታ ምክንያት ነውና ለማርታም ምስጋና ይገባታል፡፡
v  ዝናው ከሥራው በላይ የገነነበት ሰው ያልታደለ ነው፡፡
v  ኃጢአቱን ተረድቶ ንስሐ የሚገባ ኃጢአተኛ ምንም በደል ከሌለበት ነገር ግን ራሱን እንደ ጻድቅ ከሚቆጥር ሰው የበለጠ ይሻላል፡፡
v  በሽታን እንጂ በሽተኛን አትጥላ፡፡
v  ወጣትና ጤናማ ከሆንክ በድካም ለምትሸነፍበት ለእርጅናህ ዘመንም ጭምር ጹም፡፡
v  በቻልከው መጠን መንፈሳዊ ሀብትን አከማች፤ በማትችለው ጊዜ ትመነዝረው ዘንድ፡፡
v  በብዙ ሰዎች መካከል ተቀምጦ ኅሊናን ባሕታዊ ማድረግ እንዲሁም በብሕትውና ተቀምጦ በሐሳብ በከተማ ውስጥ መኖር ይቻላል፡፡
v  ከመጠን በላይ የሚመሰገንና የሚከበር ሰው ብዙ ኩነኔ ያገኟል፤ በሰው ዘንድ ከቁም ነገር ሳይቆጠር መልካም ነገርን ሠርቶ ያለፈ ሰው ግን በሰማይ ታላቅ ክብር ይጠብቋል፡፡
v  አንድ መነኰሴ ነበረ፡፡ አስቀድሞ ፍጹም የነበረ ሲሆን በኋላ ግን የትርፋቱን ነገር ቸል አለ፡፡ አንድ ቀንም አባ ኢዮብ ከተባለ ሌላ መነኰሴ ማደርያ ጐጆ ጋር ገባ፡፡ አባ ኢዮብ ያስቀመጠው ምግብንም እስከ መስረቅ ደረሰ፡፡ አባ ኢዮብም ይህንን የስርቆት ተግባር አወቀበት፡፡ ደስ ብሎትም አየው፡፡ አባ ኢዮብ በጊዜ ሞቱ ያን ሰው ጠርቶ እጆቹን ሳማቸው፤ ወደዳቸው፤ እንዲህም አለ፡- “ወንድሜ እኔስ እኒህን እጆችህን እስማቸዋለሁ፤ መንግሥተ ሰማያት የምገባበትን ምክንያት ስላመጡልኝ አመሰግናቸዋለሁአለ፡፡ ያም ሌባ መነኰሴእንዲህ የሰው መጽደቂያ ሁኛለሁንብሎ ንስሐ ገባ፡፡ እግዚአብሔር ይርዳን!!!!!!

FeedBurner FeedCount