Wednesday, May 2, 2012

ምክረ አበው ቁጥር አንድ



v ከጐደለን ይልቅ ያለን ይበልጣል፡፡
v  ተቀብሎ የማያመሰግን ከቀማኛ ይቆጠራል፡፡
v  ለንስሐ የመደብነው ጊዜ ዓለም የማትፈልገውን የዕድሜያችንን ማለቅያ መሆኑ ያሳዝናል፡፡
v  ነገሥታት በክርስቲያኖች ጸሎት ካልታገዙ ሰይጣን ሲያውካቸው ሕዝቡን ያውካሉ፡፡
v  በጠብ ውስጥ ያለ ረሀብ፣ በድሪቶ ውስጥ ያለ ጥጋብ፣ በጐፈሬ ውስጥ ያለ ጽድቅ አይታወቅም፡፡
v  እንደ ዳዊት ስንዘምር እንደ ሜልኮል የሚያሽሟጥጡ አይጠፉም፡፡
v  ሰይጣን ላያስተኛን ተኙ ይለናል፡፡
v  ማርያም የተመሰገነችው በማርታ ምክንያት ነውና ለማርታም ምስጋና ይገባታል፡፡
v  ዝናው ከሥራው በላይ የገነነበት ሰው ያልታደለ ነው፡፡
v  ኃጢአቱን ተረድቶ ንስሐ የሚገባ ኃጢአተኛ ምንም በደል ከሌለበት ነገር ግን ራሱን እንደ ጻድቅ ከሚቆጥር ሰው የበለጠ ይሻላል፡፡
v  በሽታን እንጂ በሽተኛን አትጥላ፡፡
v  ወጣትና ጤናማ ከሆንክ በድካም ለምትሸነፍበት ለእርጅናህ ዘመንም ጭምር ጹም፡፡
v  በቻልከው መጠን መንፈሳዊ ሀብትን አከማች፤ በማትችለው ጊዜ ትመነዝረው ዘንድ፡፡
v  በብዙ ሰዎች መካከል ተቀምጦ ኅሊናን ባሕታዊ ማድረግ እንዲሁም በብሕትውና ተቀምጦ በሐሳብ በከተማ ውስጥ መኖር ይቻላል፡፡
v  ከመጠን በላይ የሚመሰገንና የሚከበር ሰው ብዙ ኩነኔ ያገኟል፤ በሰው ዘንድ ከቁም ነገር ሳይቆጠር መልካም ነገርን ሠርቶ ያለፈ ሰው ግን በሰማይ ታላቅ ክብር ይጠብቋል፡፡
v  አንድ መነኰሴ ነበረ፡፡ አስቀድሞ ፍጹም የነበረ ሲሆን በኋላ ግን የትርፋቱን ነገር ቸል አለ፡፡ አንድ ቀንም አባ ኢዮብ ከተባለ ሌላ መነኰሴ ማደርያ ጐጆ ጋር ገባ፡፡ አባ ኢዮብ ያስቀመጠው ምግብንም እስከ መስረቅ ደረሰ፡፡ አባ ኢዮብም ይህንን የስርቆት ተግባር አወቀበት፡፡ ደስ ብሎትም አየው፡፡ አባ ኢዮብ በጊዜ ሞቱ ያን ሰው ጠርቶ እጆቹን ሳማቸው፤ ወደዳቸው፤ እንዲህም አለ፡- “ወንድሜ እኔስ እኒህን እጆችህን እስማቸዋለሁ፤ መንግሥተ ሰማያት የምገባበትን ምክንያት ስላመጡልኝ አመሰግናቸዋለሁአለ፡፡ ያም ሌባ መነኰሴእንዲህ የሰው መጽደቂያ ሁኛለሁንብሎ ንስሐ ገባ፡፡ እግዚአብሔር ይርዳን!!!!!!

No comments:

Post a Comment

FeedBurner FeedCount