Monday, December 23, 2013

“ብርሃንካን ሐቅኻን ልአኽ ይምርሑኒ ካዓ ናብ ቅዱስ እምባኻን መሕደሪኻን ድማ ይውሰዱኒ።” መዝ.43:3



ብዲ/ን ፅጋቡ ወልዱ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታሕሳስ 14፣ 2006 ዓ.ም. ግእዝ)፡- በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን!!!
መእተዊ
 በቋንቋ ቤተክርስቲያን ወይም ብናይ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ቅድሚ በዓል ልደት ዘለዋ ሠለስተ ሰናብቲ፡- ስብከት፣ ብርሃንን ኖላዊን ብምባል ይፍለጣ፡፡ ቅድስቲ ቤተክርስቲያ ነገር ኩሉ ብግዚኡ አዝዩ ግሩም ገይሩ ንዝፈጠረ ኣምላክ ምስጋናአ ብዘመናት ከፋፊላ ምቕራብ ባህሪአ እዩ /መክ 3፣11/፡፡ ሕድሕድ ሰንበት ነናይ ባዕሉ ትምህርቲ ዝሐዘ እዩ፡፡ ካብተን ሠለስተ ሰናብቲ እተን ናይ መጨረሽታ ክልተ ማለት እውን ብርሃንን ኖላዊን እግዚአብሔር ብዝፈቐዶ መጠን ክንመሃሃር ኢና፡፡

Sunday, December 22, 2013

ነቢዩ ኢዩኤል

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፲፬ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
“ኢዩኤል” ማለት “እግዚአብሔር አምላክ ነው” ማለት ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱሳችን እንደምንመለከተውም “ኢዩኤል” የሚለው ስም በዕብራውያን የተለመደ መኾኑ ነው /፩ኛ ሳሙ.፰፡፪፣ ፩ኛ ዜና ፬፡፴፭፣ ፪ኛ ዜና ፳፱፡፲፪፣ ዕዝራ ፲፡፵፫/፡፡
 አባቱ ባቱአል እናቱም መርሱላ ይባላሉ፡፡ የመጽሐፉ የአንድምታ ትርጓሜ መቅድም እንደሚናገረው ነገዱ ከነገደ ሮቤል ወገን ነው፡፡ ሌሎች ሊቃውንት ግን ኢዩኤል ከነገደ ይሁዳ ወገን እንደኾነ ይናገራሉ፡፡ ለዚኽ አባባላቸው እንደ ማስረጃ የሚያስቀምጡትም አንደኛ ኢዩኤል ይኖር የነበረው በኢየሩሳሌም መኾኑ፤ ኹለተኛ በመጽሐፉ ስለ ካህናት ማንሣቱ /፩፡፲፫/፤ ሦስተኛ ስለ ቤተ መቅደስ መናገሩ /፩፡፱/፣ እና ሌላም ሌላም በማለት ነው፡፡

Friday, December 20, 2013

ነቢዩ ሚክያስ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፲፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
“ሚክያስ” ማለት “መኑ ከመ እግዚአብሔር - እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው?” ማለት ነው፡፡ ይኸውም ተልእኮውን የሚያስረዳ ነው፡፡ ምክንያቱም መጽሐፉን ስናነብ የሚከተሉትን እንገነዘባለንና፡-

Tuesday, December 17, 2013

ነቢዩ አሞጽ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፱ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
“አሞጽ” ማለት “ሽክም፣ ጭነት” ማለት ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ በዚኽ ስም የሚጠሩ ሦስት ሰዎች ያሉ ሲኾን እነርሱም የነቢዩ ኢሳይያስ አባት /ኢሳ.፩፡፩/፣ የምናሴ ልጅ ንጉሥ አሞጽ /፪ኛ ነገ.፳፩፡፲፰/ እንዲኹም ለዛሬ የምናየውና ከደቂቀ ነቢያት አንዱ የኾነው ነቢዩ አሞጽ ናቸው፡፡
 የቤተ ክርስቲያናችን ትውፊት እንደሚያስረዳው የነቢዩ አሞጽ አባት ቴና ሲባል እናቱ ደግሞ ሜስታ ትባላለች፡፡ ነገዱም ከነገደ ስምዖን ወገን ነው፡፡

FeedBurner FeedCount