Monday, April 7, 2014

ኒቆዲሞስ ዘሠኑይ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 29 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ሰው በመሆናችን ልንሸከመው የማንችለውን ፍቅር ሰጠኸን፤ በጨለማ ሆነን አንተን ስንናፍቅ የማይጨልም ብርሃንን በሕይወታችን አበራህልን፤ የልባችንን ፍሬ መራራነት ታገስከን፤ የማስመሰላችንን ድራማ ቸል አልክልን፤ ስምህን ባጎደፍነው መጠን ሳይሆን በማይለካው ፍቅርህ ንጽሕናን አለበስከን፤ ፍቅርና ሰላም የለም ብለን ተስፋ በቆረጥን ጊዜ ይህ ነው በማይባል ሰዓት ደርሰህ እኛ የምንገረምበት እኛነት አደልከን፤ ሰላምን አጎናጸፍከን፤ በዚህ ሰላም ለሁላችሁ ሰላም ይሁን::

Saturday, April 5, 2014

ኒቆዲሞስ ዘሰንበተ ክርስቲያን



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 27 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በሕልውና አንድ በሚሆን ሦስት፣ የማያገኙት ከፍ ያለ፣ የማያዩት የተሰወረ፣ የማይዙት እሳት፣ የማይዳስሱት መንፈስ፣ በማስተዋል የማይወስኑት ኃይል፣ የማይሾሙት ንጉሥ በሆነ በእግዚአብሔር ስም በመለኮቱ አምላካችን በቸርነቱም አባታችን ነው:: ለእርሱ ምሥጋና ይሁን:: በእርሱም የሆነ ሰላም ይብዛላችሁ::

ገብር ኄር ዘቀዳሚት ሰንበት

በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 27 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በሦስትነት አንድ፣ በአንድነት ሦስት በሚሆን፣ በባሕርይ አንድ በሚሆን፣ በመለኮትም በሚተካከል በእግዚአብሔር ስም፣ በአንዲት ፈቃድ በሚተባበሩ በምሥጋና መብረቅ በተጋረዱ፣ በሚነድ እሳትም በሚሸፈኑ ጥንትና ፍጻሜ በሌለው በአንድ አምላክ ሰላም ይሁንላችሁ::

Thursday, April 3, 2014

ገብር ኄር ዘዓርብ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 25 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 እንደ ሱራፌል ቃል በምናመሰግነው፣ የሰው ልጅ በማይነካው፣ የሟችም ሕሊና በማይመረምረው፣ በጽርሐ አርያም አትሮኑሱን ያኖረ፣ በተራሮች ራስ ላይ የጉምን ተን በሚያተን፣ ያለጩኸት በሚያስወግደው፣ በአየራት ውስጥ በሚያመላልሰው፣ ሰፊውን የሰማይ ገጽ የደመና ግምጃን በሚያላብሰው፣ ክብርና ምሥጋና በሚገባው በእግዚአብሔር ስም ሰላም ለእናንተ ይሁን::

FeedBurner FeedCount