Thursday, September 6, 2012

አሮጌውን ሰው አስወግዱ


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

የዚህ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያኖች በአዲሱ ዓመት በክርስትና ሕይወታቸው እንዲያድጉ እንጂ በፊተኛ ኑሮአቸው እንዳይመላለሱ ከጨለማ ሥራ ጋርም እንዳይተባበሩ ለማሳሰብ ነው፡፡ ይህን ቃል የተናገረው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች በጻፈላቸው መልእክቱ ነው /ኤፌ.4፡23/፡፡ 

  ኤፌሶን በሮም መንግሥት ሥር ሆና ታናሽ እስያ በምትባል አውራጃ በኤጅያን ባሕር ዳር /በዛሬዋ ኢያዘሎክ-ቱርክ/ የምትገኝ ታላቅ የንግድ፣ የአምልኮና የወደብ ከተማ ነበረች፡፡ በከተማዋ አርጤምስ /በላቲኑ አጠራር- ዲያና/ ለምትባል አምላክ ትልቅ መቅደስ ታንጾ ነበር /ሐዋ.19፡24፡27/፡፡ የባሕር አሸዋ የድሮይቱን ከተማ ስለሸፈናት ዛሬ ሰው አይኖርባትም፡፡ 

   ምንም እንኳን ክርስትና ወደዚህች ከተማ የገባው በጵርስቅላና በአቂላ አማካኝነት ቢሆንም /ሐዋ.18፡18-19/ ቤተ ክርስቲያኒቱ በይፋ የተቋቋመችው ግን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሦስተኛው ጉዞው ወደዚህች ከተማ መጥቶ ለሦስት ዓመት ያህል ወንጌል ካስተማረና ብዙ ሕዝብም ወደ ክርስትና ከመለሰ በኋላ ነው /ሐዋ.19፡8-27፣ 20፡31/፡፡ 

የኤፌሶን ከተማ ጢሞቴዎስ ጵጵስና የተሾመባትና በሰማዕትነት ያረፈባት፤ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ሞትን ሳያይ የተሰወረባት፤ በኋላም በ431 ዓ.ም የንስጥሮስ ክሕደት በጉባኤ ተወግዞ የእመቤታችን ወላዲተ አምላክነት በይፋ የተመሰከረባት ከተማ ናት፡፡ 

ሐዋርያው መልእክቲቱን የጻፈላቸው ዋና ዓላማ አንደኛ የኤፌሶን ክርስቲያኖች ምንም እንኳን አሕዛብ ቢሆኑም ከእስራኤል ጋር አንድ ሆነው በክርስቶስ ጸጋ መዳናቸውንና ሰማያዊ ክብር ማግኘታቸውን አውቀው በእምነታቸው እንዲጠነክሩ ለማድረግ ሲሆን /ምዕ.1-3/ ሁለተኛው ደግሞ በክርስትና ሕይወታቸው እንዲያድጉ እንጂ በፊተኛ ኑሮአቸው እንዳይመላለሱ ከጨለማ ሥራ ጋርም እንዳይተባበሩ ለማሳሰብ ነው /ምዕ.4-5/፡፡ እኛም እግዚአብሔር እንደወደደና እንደፈቀደ በሁለተኛው ዓላማ ላይ በማተኰር እንማማራለን፡፡ ማስተዋሉን ያድለን!!

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ምዕራፍና ቁጥር “ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፤ በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፤ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ” ይላል /ኤፌ.4፡22-24/፡፡ 

   ምን ማለት ነው? አሮጌ ማለት ፊተኛ፣ የቀድሞ፣ የድሮ፣ የጥንት፣ ያረጀ ማለት ነው፡፡ ፊተኛ ኑሮ ማለትም የድሮ ባሕርይ፣ የቀድሞ ምልልስ ማለት ነው፡፡ የሰው ልጅ አሮጌነትን የተላበሰው በቀዳማዊ አዳም በደል ምክንያት ነው፡፡ ቀዳማዊ አዳም አስቀድሞ በእግዚአብሔር አርአያና አምሳል የተፈጠረ ንጽሐ ጠባይዕ ነበረው፡፡ መተዳደሪያውም ጽድቅ ብቻ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ይህን እስከ መጨረሻ መጠበቅ አልቻለም፡፡ ሐዋርያው እንደነገረን  ዲያብሎስ ከቅንአት የተነሣ /ጥበብ.1፡24/ በእባብ አካል ተሰውሮ አዳምን በሚያታልል ምኞት ተፈታተነው /ዘፍ.3፡1/፡፡ ወደ እርሱ ፈቃድ ስቦም “አትብሉ” የተባሉትን የዛፍ ፍሬ ከሚስቱ ጋር እንዲበላ አደረገው፡፡ ያን ጊዜ አዳም ከክብሩ ተዋረደ፡፡ አሮጌ ሆነ፡፡ ባሕርዩ ወደ ኃጢአት ያዘነበለ ሆነና በእርሱ ጠባይ

Tuesday, September 4, 2012

እግዚአብሔር የተወሰኑ ሰዎችን ለመንግሥቱ ሌሎችን ደግሞ ለገሃነም ወስኗልን?


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

አንዳንድ ወገኖች የሰው ዕድል ፈንታው ጽዋዕ ተርታው ከጻድቃን ወይም ከኩንኖች መሆን አስቀድሞ በእግዚአብሔር የተወሰነ ነው በማለት ይናገራሉ፡፡ ለዚህ ቅድመ ውሳኔ /Predestination/ ሐሳባቸውም አስረጅ አድርገው የሚያቀርቧቸው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅሶች አሏቸው /ሮሜ.911-21 ኤፌ.14/፡፡ ከዚህም በመነሣት ድኅነት የሚገኘው ከዘመናት በፊትእግዚአብሔር በወሰነው መሠረት እንጂ ሰው በሚፈጽመው ሥራ የማይሰጥ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ እስኪ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በዚህ ጉዳይ ምን ብላ እንደምታስተምርና የእነዚህ ሰዎች አስተምህሮ የሚያመጣው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ተፋልሶ ምን እንደሆነ እንመልከት!

             1.አስቀድሞ ሁሉን ማወቅ ወይስ አስቀድሞ መወሰን?
 እግዚአብሔር ዓለምን ከመፍጠሩ በፊት እስከ ዓለም ፍጻሜ ሊሆን ያለውን ነገር ምንም ሳይሰወርበት ሁሉን ያውቃል፡፡ አንድ ሰው ከቅዱሳን ወገን አልያም ከኃጥአን ወገን እንደሚሆን አስቀድሞ ያውቃል /ሮሜ.828-30/፡፡ ሆኖም ግን የተወሰኑትን ለመንግሥተ ሰማያት የተወሰኑትን ደግሞ ለገሃነም ለኩነኔ አልፈጠራቸውም፡፡ እንዲህ ቢሆንስ ኖሮ እግዚአብሔር አንድስ እንኳ ይጠፋ ዘንድ እንደማይፈልግ ባለተናገረ ነበር /2ጴጥ.39/ የዓለም ሕዝብ በሙሉ ለድኅነት መጥራት ባላስፈለገ ነበር /ማቴ.2819 ሮሜ.819/ ሰዎች ሁሉ ይድኑ እውነትንም ያውቋት ዘንድ ባልወደደ ነበር /1ጢሞ.24/፡፡ በመሆኑም ሰው ከእግዚአብሔር በተቀበለው ነጻ ፈቃዱ ተጠቅሞ ወይ ርትዕት በሆነች የሕይወት መንገድ ይጓዛል አሊያም የሞት መንገድ በምትሆን በኃጢአት መንገድ ይሄዳል፡፡ ድኅነት ለሁሉም የተሰጠ ቢሆንም የሰው ድኅነቱ በራሱ መሻትና የነጻ ፈቃድ ምርጫ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ሄሬኔዎስ የተባለ አባትም፡- ጥቂቶች በተፈጥሮ ክፉ ቢሆኑ ሌሎችም መልካም ቢሆኑ መልካሞቹ ስለ መልካምነታቸው መልካም ሠሩ ተብለው ምስጋና የተገባቸው አይሆኑም፡፡ ሲፈጠሩ እንዲህ ሆነው ነውና፡፡ ክፉዎቹም ስለ ክፋታቸው ነቀፌታን ባላገኛቸው ነበር፡፡ ጥንቱንም ሲፈጠሩ እንዲህ ሆነዋልና ብሏል /Iraneus, Book IV, Chap.37/፡፡ 

             2. እግዚአብሔር አያዳላም ፍርዱም ርቱዕ ነው!
 እግዚአብሔር የተወሰኑ ሰዎችን ለመንግሥተ ሰማያት ሌሎችን ደግሞ ለገሃነም አስቀድሞ ወስኗል ማለት ክብር ምስጋና ለስም አጠራሩ ይሁንና እግዚአብሔር ያዳላል እንደማለት ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ግን አምላካችሁ እግዚአብሔር የአማልክት አምላክ፣ የጌቶች ጌታ፣ ታላቅ አምላክ፣ ኃያልም፣ የሚያስፈራም፣ በፍርዱም የማያዳላ፣ መማለጃም የማይቀበል ነው /ዘዳ.1017/ እግዚአብሔር ለሰው ፊት እንደማያዳላ በእውነት አየሁ /ሐዋ.1034/ ከእግዚአብሔር ዋጋችሁን እንደምትቀበሉ ታውቃላችሁ፤ ለክርስቶስ ትገዛላችሁና፤ የሚበድል ግን ፍዳውን ያገኛል እርሱም አያደላለትም ይላል /ቈላ.323/፡፡  

           3.አስቀድሞ መወሰን አለ ከተባለ ትእዛዛት ለምን ተሰጡ?
 እግዚአብሔር የተወሰኑትን ሰዎች ለመንግሥተ ሰማያት የተወሰኑትን ደግሞ ለገሃነም ፈጠረ ከተባለ ሰዎች በአእምሮ ጠባይ መሪነት፣ በሥነ ፍጥረት አስተማሪነት፣ በሕገ ልቡና አዋቂነት መልካም ሥራ መሥራት

Monday, September 3, 2012

እኔም አልፈርድብሽም- የዮሐንስ ወንጌል የ36ኛ ሳምንት ጥናት(8፡1-11)


 
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
  ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አይሁድ ከሚያከብሩት የዳስ በዓል በኋለኛው ቀን “ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ፡፡ በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ የሕይወትን ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል” ብሎ አሰምቶ ከነገራቸው በኋላ፣ አለቆቹና ካህናትም ክርክራቸውን ከፈጸሙ በኋላ /7፡53/ “ወደ ደብረ ዘይት ሄደ” /ቁ.1/። ካስተማርን፣ ከገሰጽን፣ ከመከርን በኋላ የራሳችን የሆነ የጽሞናና የጸሎት ጊዜ ሊኖረን እንደሚገባ ሲያስተምረን አንድም ማደርያው በዚያ ነበርና ወደ ደብረ ዘይት ሄደ /St. John Chrysostom/፡፡

  ከዚያ ሲጸልይ አድሮም እንደ ልማዱ ገስግሶ ወደ መቅደስ ሄደ /ቁ.2/፡፡  የመልካም አገልጋይ ባሕርይ እንዲህ ነው፡፡ መልካም አገልጋይ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል አገልግሎቱን በፍቅር ይፈጽማል፡፡ ስለዚህ ጌታ የሚወዳቸውን ልጆቹ ያገኝ ዘንድ ወደ ምኵራብ ገባ፡፡ “ሕዝቡም ሁሉ ወደ እርሱ ተሰበሰቡ”፡፡ ወንጌላዊው ሉቃስ “ሕዝቡም ሁሉ ይሰሙት ዘንድ ማልደው በመቅደስ ወደ እርሱ ይመጡ ነበር” እንዲል ትምህርቱን ያስተምራቸው ጀመር /ሉቃ.21፡38/፡፡

   በዚህ ጊዜ ጸሐፍትና ፈሪሳውያን ሕዝቡ የጌታን ትምህርት ያደምጡ ዘንድ እንዴት በጧቱ እንደተሰበሰቡ አዩ፡፡ ውስጣቸውም በቅንአት ተቃጠለና ትምህርቱን ያደናቅፉ ዘንድ ስትሴስን ያገኟትን አንዲት ሴት አስረው ይዘዋት መጡ፡፡ አምጥተውም ጌታ ካለበት ጉባኤ መካከል አቆሟት /ቁ.3/፡፡ ከዚያም “መምህር ሆይ!” ይሉታል /ቁ.4/፡፡ መምህርነቱን አምነውበት አልነበረም /7፡47/፡፡ አመጣጣቸው ለተንኰል ስለ ነበር እንጂ፡፡ ስለዚህ “ይህች ሴት ስታመነዝር ስትሴስን ተገኝታ ተያዘች (አግኝተን ያዝናት)፡፡ ሙሴም እንደዚህ ያሉት (አንድ ወንድ ለአንድ ሴት፤ አንዲት ሴት ለአንድ ወንድ ይሁን የሚለውን ሕግ ተላልፈው ቢገኙ) እንዲወገሩ አዘዘን፤ አንተስ ምን ትላለህ (ምን ትፈርዳለህ)?” አሉት /ቁ.5/፡፡  እንደነርሱ ሐሳብ ይህች ሴት ስትሴስን ስለ ተገኘች በዚህ ምድር በሕይወት መኖር “የማይገባት” ሴት ነች፡፡ የሚደንቀው ግን ይዘዋት የመጡት ወደ ይቅርታ አባቷ ወደ እግዚአብሔር መሆኑን አለማወቃቸው ነው፡፡ ይዘዋት የመጡት በዓለም ላይ እንዲፈርድ ሳይሆን ዓለምን እንዲያድን ወደ መጣው ጌታዋ

Thursday, August 30, 2012

ኣረጊት ሰብነትኩም ቐንጥጡ


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

 ናይ’ዚ ትምህርቲ’ዚ መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያን ሰባት ኣብ ሂወቶም መሠረታዊ ለውጢ ንኸምጽኡ ምብርትታዕ እዩ፡፡

  ኣብ ሂወትና ተለዊጦም ክንሪኦም እንደሊ ብዙሓት ነገራት አለዉ፡፡ ዓይነቶም ከዓ ከከም መልክዕና ዝተፈላለዩ እዮም፡፡ ገሌና ደመወዝና ክልወጥ ንደሊ፤ ገሌና ባህርያትና ተመሓይሹ ክንርኢ ንደሊ፤ ገሌና ምስ ካልኦት ሰባት ዘለና ሕርፉፍ ምቅርራብ ተለዊጡ ክንርኢ ንደሊ፤ ገሌና ሓዳርና ስሙር ኮይኑ ክንርኢ ንደሊ፤ ገሌና ሕማቕ እንዳተዛረብና ንሰባት ንቱግ ኢልና እንዳተፃረፍና ተሸጊርና ንኾን፡፡ ኮታስ ብዙሕ ተለዊጦም ክንሪኦም እንደሊ ነገራት ኣለዉ፡፡ እዞም ተለዊጦም ክንሪኦም እንደልዮም ነገራት ተለዊጦም ንምርኣይ ብዙሕ ፃዕሪ ጌርና ንኸውን፡፡ እዚኣቶም ተለዊጦም ንምርኣይ ብዓል ሙያ ኣማኺርና ንኸውን፤ ብዙሓት መጻሕፍቲ ገዚእና ኣንቢብና ንኸውን፤ ብዙሕ ግዜ ንኣምላኽ ለሚንናዮ ንኸውን፡፡ ስለዘይተለወጥና ኸዓ ተስፋ ቖሪፅና ንኸውን፡፡ ለውጢ ምምፃእ ኣብ ህይወትና እቲ ዝኸበደ ነገር ኮይኑ ተሰሚዑና ክኸውን ይኽእል እዩ፡፡

 “ንምንታይ ኣይተለወጥኩን? ንምንታይ ኣምላኽ ፀሎተይ አይሰምዐን?” ኢልና ምሕታት አገዳሲ ጥራሕ ዘይኮነስ ግድን እዩ፡፡ ከምዚ ኢልና እንትንሓትት ፀገምና አበየናይ ቦታ ከምዝነበረ ንምእላሽ መፍትሒኡ እውን ንምንዳይ ኸቢድ ስለዘይኮነ፡፡ እስኪ ንሂወት ያዕቆብ ወዲ ይስሓቕ ብምልዓል እቲ ናሃትና ፀገም ኣበይ ከም ዘሎ ንፈትሾ!

1. ሰብ ሞያ ጥዕና ናይ ሓደ ሰብ ሕማም እንታይ ምኻኑ ምፍላጥ ናይ ሕክምና 50 ምኢታዊ እዩ ይብሉ፡፡ ብመንፅር ክርስትና ከዓ ኣረኣእያ ሰብን ኣረኣእያ እግዚአብሄርን ዝተፈላለየ ስለዝኾነ እግዚኣብሄር በቲ ዝጠቕመና መኣዝን እንትጅምር ንሕና ድማ ኣይኾንን ኢልና በኣንፃሩ ኬድና ክንከውን ንኽእል ኢና፡፡ ንሕና እንሪኦ ደጋዊ መልክዕ እንትኸውን እግዚኣብሄር ግና እቲ ውሽጣዊ ፅባቐ ይርኢ፡፡ እዙይ እውን ካብ ቃል ኣምላኽ ክንርዳእ ንኽእል፡፡ “ኣነ እግዚኣብሄር ከም ኣረኣእያ ሰብ ኣይርእን እየ፡፡ ሰብ ነቲ ኣብ ቅድሚ ዓይኑ ዘሎ እዩ ዝርኢ፤ ኣነ እግዚኣብሄር ግና ልቢ እየ ዝርኢ” ይብል /1ሳሙ.16፡7/፡፡ ስለዚ እቲ ናህና ሕቶ ኣበይ ነበረ? ውሽጥና ንኽልወጥ

FeedBurner FeedCount