Sunday, September 30, 2012

ከሰው ይልቅ እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት


አባታችን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በጊዜው የነበረችው ጨካኝ ንግሥት (ኤውዶክስያ) በክፋት ተነሣስታ በመንፈቀ ሌሊት አስጠርታ በፈረስ በሠረገላ አድርጋ ወደ ደሴተ አጥራክያ ስታግዘው ለራሱ እንዲህ አለ፡- ንግሥቲቱ ከከተማ ስታስወጣኝ ምንም ዓይነት ንዴት አልተሰማኝም፤ ይልቁንም ለራሴ እንዲህ አልኩ እንጂ፡-

Thursday, September 27, 2012

የዕርቅ ቀን


    በእግረ ሕሊናችሁ ከአዲስ አበባ በሰሜን አቅጣጫ 1010 ኪ/ሜ ልውሰዳችሁ፡፡ የጠቀስኩላችሁን ያህል ርቀት ስትጓዙ ዓድዋ ከተማ ትደርሳላችሁ፡፡ ዓድዋ ማለት “ኦድዋ” ከሚል የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ከበብዋት ማለት ነው፡፡ ከተማዋ ይህን ስም ያገኘችው ዙርያዋ በተስዓቱ ቅዱሳን ገዳማት የተከበበች ስለሆነ እንደሆነ ይነገራል፡፡ አጠገብዋም ዓዲ አቡን - የአቡን ሀገር የምትባል ሌላ ከተማ አለች፡፡ እዚያ አከባቢ ብቻ የሚበቅል ቲማቲም መሰል አትክልት አለ፡፡ ስሙም “ጸብሒ አቡን” ይባላል፡፡ የአቡን ወጥ እንደማለት ነው፡፡

Wednesday, September 26, 2012

መስቀል ኃይላችን ነው



ከጌታችን ስቅለት በፊት መስቀል መቅጫ ነበር፡፡ ሰውን በመስቀል መስቀል የጀመሩት ፋርሳውያን ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎችኦርሙዝድየሚባል የመሬት አምላክ ስለበራቸው እርሱን ላለማርከስ ብለው ወንጀለኛውን ሁሉ ከመሬት ከፍ አድርገው ሰቅለው ይቀጡት ነበር፡፡ በኋላም ይህ አድራጎት በሮማውያን ግዛት ሁሉ ሕግ ሆነ፡፡
በኦሪቱ ሥርዓትም በመስቀል የሚቀጡ ርጉማን ውጉዛን ነበሩ፡፡ ከጌታችን ስቅለት በኋላ ግን የነጻነታችን አርማ የድል ምልክታችን ሆነ፡፡ ክርስቶስ ይህን መስቀል ዙፋኑ አድርጎ ሰላምን እኩልነትን አድርጓልና፡፡ ስለዚህ ካሉን ነገሮች ሁሉ መስቀል የላቀ ክብር አለው፡፡

Monday, September 24, 2012

MESKEL IN ETHIOPIA



In The Name of The Father, The Son; & The Holy Spirit One God Amen!!

The word Meskel has two meanings. One literal meaning is the Holy Cross. The other meaning is the Feast of the Holy Cross; an event which is annually celebrated in Ethiopia in commemoration of the finding of the Holy Cross. The Holy Cross is very significant in the Ethiopian Orthodox Tewahdo Church (EOTC). The founding father of EOTC hymn, St. Yared, says in his composition hymn book ‘MERAF’ that the Holy Cross is above everything else in the Church. He says ‘It saves us from our enemy; the devil. It is true that the Holy Cross has saved the entire world.’

FeedBurner FeedCount