Tuesday, April 8, 2014

ሆሳዕና ዘሰንበተ ክርስቲያን



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 4 ቀን 2006 ዓ.ም)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በዋዜማው ማለትም ቅዳሜ ማታ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ለማኅሌት ደውል ከተደወለ በኋላ ይገባሉ:: ከቅዱስ ያሬድ መጽሐፍትና ከሌሎችም በመላእክት ዜማ ዕለቱን የሚያነሳ ቀለም (ትምህርት) እያነሱ ያድራሉ:: ከዚህ በኋላ ጠዋት ለቅዳሴ ሰዓቱ ሲደርስ ሊቃውንቱተበሀሉ ሕዝብ በበይናቲሆሙ እንዘ ይብሉ ዓይ ውእቱ ዝንቱ ንጉሠ ስብሐት እስመ ውእቱ እግዚአ ለሰንበት ቦአ ሃገረ ኢየሩሳሌም በፍስሐ ወበሰላም- ሕዝቡም እርስ በእርሳቸው ተባባሉ እንዲህ እያሉ ይህ የምሥጋና ንጉሥ ማነው? እርሱ የሰንበት ጌታ ነውና፤ በደስታና በሰላም ወደ ኢየሩሳሌም ሃገር ገባ::” የሚለውን የዕለቱን የጾመ ድጓ ክፍል ይቃኛሉ::

ኒቆዲሞስ ዘቀዳሚት ሰንበት (ሆሳዕና)



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 3 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በአብና በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም፣ አንድ የናዝራውያን አምላክ፣ የማይለወጥ የሃይማኖት ምሰሶ፣ የማይፍገመገም የመርከባችን አለቃ፣ የማይጨልም የፋናችን ብርሃን፣ ከዘመናት በፊት በሕልውና አንድ የሆነ፣ በስምና በሥልጣን የሠለጠነ፣ የመለኮቱ አንድነት የማይለወጥ፣ የመንግሥቱ ስፋት የማይወሰን፣ የብልጥግናው ክብደት የማይለካ እርሱ በሰላም ይጠብቀን::

ኒቆዲሞስ ዘዓርብ (ሆሳዕና)



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 2 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በአንድነት በሚመሰገን፣ በአንድነትም በሚለመን፣ በአንድነት በሚሰበክ፣ አንደበት ሁሉ የሚገዛለት፣ ጉልበትም ሁሉ የሚሰግድለት፣ ምሥጉን አምላክ በሆነ በእግዚአብሔር ስም፣ በመጽሐፍ ራስ ሁሉ ላይ በጥበብ ቁጥር በእርሱ ስምና በመስቀሉ ምልክት በማማተብ ሰላምታ ይድረሳችሁ:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

ኒቆዲሞስ ዘሐሙስ (ሆሳዕና)



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 1 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ዙፋኑን በሚንቦገቦግ የእሳት ሰረገላ ላይ ያደረገ፣ በእሳት መጋረጃዎች የሚሰወር፣ በምሥጋናም መብረቅ የሚጋረድ፣ በኪሩቤል የሚመሰገን፣ በሱራፌልም የሚወደስ እስራኤል ያመሰገኑት አንድ አምላክ በሥልጣንና በቻይነት የሰለጠነ በሆነ በእግዚአብሔር ስም ሰላም ይሁንላችሁ:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

FeedBurner FeedCount