Saturday, April 12, 2014

ሰሙነ ሕማማት



በሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 5 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት እጅግ ከሚወደዱ እና ከሚናፈቁ ወቅቶች አንዱ ሰሙነ ሕማማት ነው፡፡ በዕለተ ሆሳዕና ጀምሮ በዕለተ ትንሣኤ የሚጠናቀቀው እጅግ ላቅ ያለ መንፈሳዊ ሕይወት የሚታይበት ጊዜ ነው፡፡ በላቲን Hebdomas Sancta or Hebdomas Maior በግሪክ ደግሞ γία κα Μεγάλη βδομάς, Hagia kai Megale Hebdomas  ታላቁ ሳምንት ተብሎ ይጠራል፡፡ በኛ ደግሞ ሰሙነ ሕማማት፡፡

Tuesday, April 8, 2014

ሆሳዕና ዘሰንበተ ክርስቲያን



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 4 ቀን 2006 ዓ.ም)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በዋዜማው ማለትም ቅዳሜ ማታ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ለማኅሌት ደውል ከተደወለ በኋላ ይገባሉ:: ከቅዱስ ያሬድ መጽሐፍትና ከሌሎችም በመላእክት ዜማ ዕለቱን የሚያነሳ ቀለም (ትምህርት) እያነሱ ያድራሉ:: ከዚህ በኋላ ጠዋት ለቅዳሴ ሰዓቱ ሲደርስ ሊቃውንቱተበሀሉ ሕዝብ በበይናቲሆሙ እንዘ ይብሉ ዓይ ውእቱ ዝንቱ ንጉሠ ስብሐት እስመ ውእቱ እግዚአ ለሰንበት ቦአ ሃገረ ኢየሩሳሌም በፍስሐ ወበሰላም- ሕዝቡም እርስ በእርሳቸው ተባባሉ እንዲህ እያሉ ይህ የምሥጋና ንጉሥ ማነው? እርሱ የሰንበት ጌታ ነውና፤ በደስታና በሰላም ወደ ኢየሩሳሌም ሃገር ገባ::” የሚለውን የዕለቱን የጾመ ድጓ ክፍል ይቃኛሉ::

ኒቆዲሞስ ዘቀዳሚት ሰንበት (ሆሳዕና)



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 3 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በአብና በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም፣ አንድ የናዝራውያን አምላክ፣ የማይለወጥ የሃይማኖት ምሰሶ፣ የማይፍገመገም የመርከባችን አለቃ፣ የማይጨልም የፋናችን ብርሃን፣ ከዘመናት በፊት በሕልውና አንድ የሆነ፣ በስምና በሥልጣን የሠለጠነ፣ የመለኮቱ አንድነት የማይለወጥ፣ የመንግሥቱ ስፋት የማይወሰን፣ የብልጥግናው ክብደት የማይለካ እርሱ በሰላም ይጠብቀን::

ኒቆዲሞስ ዘዓርብ (ሆሳዕና)



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 2 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በአንድነት በሚመሰገን፣ በአንድነትም በሚለመን፣ በአንድነት በሚሰበክ፣ አንደበት ሁሉ የሚገዛለት፣ ጉልበትም ሁሉ የሚሰግድለት፣ ምሥጉን አምላክ በሆነ በእግዚአብሔር ስም፣ በመጽሐፍ ራስ ሁሉ ላይ በጥበብ ቁጥር በእርሱ ስምና በመስቀሉ ምልክት በማማተብ ሰላምታ ይድረሳችሁ:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

FeedBurner FeedCount