Monday, May 5, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - ክፍል ፬



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፳፯ ቀን፣ ፳፻፮ ..)- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


3. ተቀምጠናል

 ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አኹን በክበበ ትስብእት ያለው በምድር ሳይኾን በሰማያዊው ስፍራ ነው፡፡ ክርስቶስ ያለው በባሕርይ አባቱ ዕሪና ተቀምጦ ነው፡፡ እኛም፡- “ወአንሥአነ ወአንበረነ ምስሌሁ በሰማያት በኢየሱስ ክርስቶስ - ከእርሱ ጋር አስነሣን፤ በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን” እንዲል ከእርሱ ጋር ተዋሕደን ስለተነሣን ያለነው በሰማያዊ ስፍራ ነው ማለት ነው /ኤፌ.፪፡፯/፡፡ ክርስቶስ ኢየሱስ ተቀመጠ መባሉ የእኛን መቀመጥ መናገሩ ነው፤ ዳግም ከውኃና ከመንፈስ ስንወለድ የእርሱ ሕዋሳት ኾነናልና፡፡ ስለዚኽ ከክርስቶስ ጋር ተዋሕደን ለመኖር ትንሣኤ ልቡናን ከተነሣን በኋላ ሰማያዊ ግብራችንን ትተን በምድራዊ ግብር ብቻ መያዝ ክርስቲያናዊ ተፈጥሯችን አይደለም፡፡ ክርስቲያናዊ ተፈጥሯችንን ካልለቀቅን በስተቀር ይኽን ማድረግ አንችልም፡፡  

Friday, May 2, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - ክፍል ፫

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፳፭ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
2.    ተነሥተናል
   ሐዋርያው፡- “ሞታችኋልና” ብሎ አላቆመም፤ ጨምሮም፡- “እንግዲኽ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችኁ” በማለት እንደተነሣንም ነገረን እንጂ፡፡ በጥምቀት ውኃ ሞቱን በሚመስል ሞት ስንሞት፥ አሮጌው ሰውነታችን እንደ ግብጻውያን ተቀብሮ ቀርቷል፡፡ አዲሱ ሰውነታችን ግን እስራኤላውያን ባሕሩ ተከፍሎላቸው እንደተሻገሩ ተሻግሯል (ተነሥቷል)፡፡ ብልየት ያለበት የቀዳማዊ አዳም ሰውነታችን በግብረ መንፈስ ቅዱስ ተቀብሮ አዲሱ ሰውነታችን ሕይወትን አግኝቶ ተነሥቷል፡፡ መሬታዊው ሰዋችን ሞቶ ሰማያዊው ሰዋችንን ለብሰን መንፈሳውያን ኾነናል፡፡ ወደ ጥንተ ተፈጥሯችን ተመልሰናል፡፡

Wednesday, April 30, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - ክፍል ፪



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፳፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! በክፍል ፩ ትምህርታችን ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ ባለው እሑድ ለምን ሱባኤ እንደማይገባ፣ ሰይጣን ይኽን ዓላማ እንዴት እንድንስተው እንዳደረገን፣ በመጨረሻም ይኽን የዲያብሎስን ደባ እንደምን ከንቱ ማድረግ ይቻለናል የሚል ጥያቄ አንሥተን ነበር ያቆምነው፡፡ እስኪ ካቆምንበት እንቀጥልና ለዚኽ ይረዳን ዘንድ አንድ ኃይለ ቃልን መነሻ በማድረግ ለመማማር እንሞክር፡፡ እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን፡፡ አሜን!!!

Monday, April 28, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - ክፍል ፩

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፲፱ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
  የዚኽ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያኖች ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ ባለው ወራት ውስጥ መንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዳይቀዘቅዝ ማበረታታት ነው፡፡
  በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ እሑድ ባለው ወራት ረቡዕንና ዓርብን ጨምሮ አይጦምም፤ አይሰገድምም፡፡ ይኽም ሠለስቱ ምዕት በ፫፻፳፭ ዓ.ም. በጉባኤ ኒቅያ ሲሰበሰቡ በኻያኛው ቀኖኗቸው የወሰኑት ቀኖና ነው /ሃይ.አበ.፳፡፳፮፣ The Oxford Dictionary of the Christian Church, pp 1250, 1738/፡፡ ይኽን ቀኖና ሲወስኑም ያለ ምክንያት አይደለም፤ ይኽ ወራት ከትንሣኤ ዘጉባኤ በኋላ ያለውን ሕይወታችን የሚያሳይ ስለኾነ ነው እንጂ፡፡ ከትንሣኤ ዘጉባኤ በኋላ ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ ለማስገዛት ተብሎ የሚደረግ ጦምም ኾነ ስግደት የለም፡፡ ሥጋ ሙሉ በሙሉ በዲያብሎስ ከመፈተን፣ ከእግዚአብሔር ውጪ የኾነ ሌላ ሐሳብን ከማሰብ ነጻ የሚወጣበት ወራት ነው፡፡ በዚያ ሰዓት ፈቃደ ሥጋ ከፈቃደ ነፍስ ጋር የተስማማ ነው፡፡ ሥጋ ሙሉ ለሙሉ ከድካሙ ነጻ ስለሚኾን እግዚአብሔርን ለማመስገን ትጉኅ ነው፡፡ እንደ አኹኑ እንቅልፍ እንቅልፍ አይለውም፤ ዘወትር የቅዱሳን መላእክትን ምግብ ለመብላት ማለትም ለማመስገን የተዘጋጀ ነው እንጂ፡፡

FeedBurner FeedCount