Thursday, December 4, 2014

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (ደረጃ ሁለት)



በዲ/ን ሳምሶን ወርቁ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ኅዳር 25 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ከዓለማዊ መሻት መለየት
 የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንዴት ሰነበታችሁ? ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ በሚለው ጽሁፍ ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ  በያዕቆብ ምናባዊ መሰላል ደረጃ ለዓለም ጀርባ መስጠት የመጀመሪያ መሆኑን ተመልክተናል፡፡ በዚህ ያዕቆብ በራዕይ በተመለከተው ምናባዊ መሰላል ላይ እግራችን መውጣት ጀምሯል፡፡ አሁን ለዓለም ጀርባ ስለሰጠን አይኖቻቸን ወደ እግዚአብሔር የሚመለከቱ ጆሮዎቻችን ድምጹን ለመስማት የሚቀኑ መሆን ይጀምራሉ፡፡ ምንያቱም ለዓለም ጀርባ ስለሰጠን ኃጢአትን መጥላት፣ የእግዚአብሔርን ፍቅሩንና ቸርነቱን መረዳት ጀምረናል፡፡ አሁን በእውነት እኛ ወደ እግዚአብሔር በማደርገው ጉዞ እንደርስ ይሆን የሚል ስጋት አይገባንም ምክንያቱም እኛ እስከፈቀድን ድረስ ከድካማችን ሊያሳርፈን ከወደቅንበት የሚያነሳን አምላክ ሊረዳን እንደቀረበ አውቀን ተረድተናልና፡፡ አሁን ጥያቄው እንዴት በመንገዳችን ጸንተን እንጓዝ የሚል ነው?

Tuesday, December 2, 2014

ስለ እመቤታችን ልደት (ለሕፃናትና ዠማሪዎች)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ኅዳር 23 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት ሰነበታችኁ? እግዚአብሔር ይመስገን ደኅና ነን አላችኁ? አሜን፡፡ እኔም በጣም ደኅና ነኝ እግዚአብሔር ይመስገን፡፡
 ልጆች! ባለፈው ጊዜ ስለምን እንደተማማርን ታስታውሳላችኁ? አቤል እና ቃየን ስለሚባሉ ኹለት ወንድማማቾች አይደል? ጐበዞች! ትክክል ናችኁ፡፡ ዛሬ ደግሞ ኹላችንም ስለምንወዳት ስለ እናታችን ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት እነግራችኋለኹ፡፡ ለመስማት ዝግጁ ናችኁ አይደል? ጐበዞች፡፡ እግዚአብሔር ዕውቀቱን ይግለጥልን፡፡ አሜን!!!

Saturday, November 15, 2014

አብሬሽ ልመለስ



በዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ቅዳሜ ኅዳር 6 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ከክብር ማረፊያው ከገሊላው ቤትሽ
ሰማሁ መፍለስሽን ወደ ግብጽ ወደ ኩሽ
ፀሐይ ሲያከትራት ያቺን የበረሃ ዖፍ
ጼዋዌን ስትናፍቅ ላንዲት ቅጽበት ሳታርፍ
ሰማሁኝ ስደቷን መጠጊያ ሳታገኝ በልቤ ላይ ስታልፍ

Wednesday, November 12, 2014

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (ደረጃ አንድ)

በዲ/ ሳምሶን ወርቁ

  (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ኅዳር ቀን፣ ፳፻፯ ..)- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 
ለዓለም ጀርባችንን እንስጥ

 እግዚአብሔር ለሰው እውቀትና ነጻ ፈቃድ ሰጥቶ አክብሮ ፈጠረው፡፡ አንዳንዶች ነጻ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው እውነተኛ የእግዚአብሔር ወዳጅ ሆኑ፤ አንዳንዶች በስንፍናቸው ነጻ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው ልግመኛ ክፉ አገልጋይ ሆኑ፡፡
ቅዱስ ዮሐንስእኔ ከየትኛው ነው የምመደበው? ከእውነተኞቹ አገልጋዮች ወይስ ከሀሰተኞቹ?” ብለን ራሳችንን እንጠይቅ ይለናል፡፡ የተጠመቀ ሁሉ የእግዚአብሔር መንግሥት ወራሽ አይደለም፣በጠባቡ ደጅ የሚገባ ሁሉ በጽናት ላይጓዝ ይችላል (ማቴ 713)፡፡ መጠመቃችን በራሱ ብቻውን ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባታችን ዋስትና አይደለም፡፡ ጥምቀት (ከኃጢያትና በኃጢአት ከመጣብን ፍዳ መዳን) ወደ ድኅነት የመግቢያ በር እንጂ ብቻውን የድኅነት መደምደሚያ አይደለም፡፡ መንፈሳዊ ሕይወትን መጀመራችን በራሱ ፍጻሜአችንን መልካም ያደርጋል ለማለት አያስችለንም፡፡  ይህ ማለት ያመነ ሊክድ ያወቀ ሊጠራጠር እና በጎ አገልጋይ ወደ ክፉ ባሪያነት ሊለወጥ የሚችልበት እድል ዘወትር አለ፡፡ አንዳንዶች በመጠመቃቸው ብቻ እንደሚድኑ የሚያስቡ አሉ፡፡ ነገር ግን ጥምቀት ብቻውን ከእግዚአብሔር የተገባልንን ቃልኪዳን አያስጠብቅልንም፡፡ ስለዚህ የመንፈሳዊ ሕይወታችንን ትክክለኛ አቅጣጫ ልንመለከት ልንመረምር ይገባል፡፡ማንም ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማይ አይገባም የአባቴን ፈቃድ የሚፈጽም እንጂእንዲል (ማቴ 721)፡፡

FeedBurner FeedCount