Thursday, January 9, 2014

ለመላው ኦርቶዶክሳውያን ፦ ታላላቅ የአንድነት የስብከትና የዝማሬ ጉባኤያትን ስለማዘጋጀት - ጥቆማ



በታምራት ፍሰሓ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥር ፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- ኦርቶዶክሳዊት እምነታችን በብዙ መስክ (በቅዳሴ በማህሌት በሰአታት በሰርክ ጉባኤያት በበዓላት ዝግጅቶች) በልዩ ስርአት ወጥነት ሐዋርያዊ መሰረተ እምነቷን ለምእመናን ስታስተላልፍ ቆይታለች አሁንም በማስተላለፍ ላይ ትገኛለች፤ በቅዳሴው ለተካፈለ በማህሌቱም ለተሳተፈ በሰአታቱም ለተገኘ በሰርክ ጉባኤውም ላልቀረ ይህ እሙን ነው፡፡ ነገር ግን ስንቶቻችን በነዚህ ተገኘን? ካልተገኘንስ እንደምን እምነታችንን ልናውቅ በእምነታችንስ ልንፀና ይቻለናል?

ብዙወቻችን ደግሞ የቤተክርስቲያን ታላላቅ በዓላትን (ደመራ ጥምቀት) መሰረት በማድረግ ተገኝተን እናከብራለን ይህም በጣም ብዙ ኦርቶዶክሳዊ በአንድነት የሚገናኙባቸው ክስተቶች ቢሆኑም ነገር ግን እኒህ ልዩ በዓላት እንደመሆናቸው የራሳቸው የሆነ የአከባበር ስርአትና ይዘት ያላቸው በመሆኑ በዚህ ጊዜ ለሚገኙ ምእመናን የሚገባውን ያህል ትምህርት ሰጥተው የሚያልፉ አይደለም ይልቅስ በነዚህ በዓላት ጥቂት ከመዘመርና በዓሉን የመታዘብ ያክል ከተመለከትን በኅላ ወደቤታችንም ሆነ ወደሌሎች ጉዳዮች የምንመለስ ብዙወች ነን፡፡ ስለዚህም ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ በአንድነት ተሰባስበን የቤተክርስቲያናችንን ስብከቷን ዝማሬዋንም ሆነ ልዩ ልዩ ሃሳቦቿን የምንረዳባቸው የምንሳተፍባቸውና የምንወያይባቸው መድረኮች የሉንም፡፡

Friday, January 3, 2014

ትምህርቲ ኖሎት



ብዲ/ን ፅጋቡ ወልዱ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታሕሳስ ፳፮፣ ፳፻፮ ዓ.ም. ግእዝ)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅደስ አምላክ

 ነገራት በብጊዜኦም ከፋፋሊት፣ ከም ውሕሉል ከሻኒ ምግቢ በብመልክዕ ንሐንጎልና ብዝምጥን መንፈሳዊን እዋናውን አስተምህሮ ምምሃር ልማዳኾነ ቅድስቲ ቤተክርስቲያን በብሰሙኑ ነናይ ባዕሎም ትምህርቲ ሰናብቲ እትውንን ተመርሚራ ይትውዲእ ቤተክርስቲያን እያ፡፡
ኣብ ዝሓለፈ ሰሙን ፅልመት ዓለምወገድ ሐቀኛ ብርሃን ነብያት ተስፋ እንዳገበርዎ ከምዝነበሩን ፅልመት ዓለም ንከወግድ ከምዝመፀ ብሐፂሩ ተመልኪትና ነይርና፡፡ ሎሚ ድማ ቅድሚ ልደት ካብ ዘለው ሰለስተ ሰናብቲ እቲ ሳልሳይ ማለት እውን ኖሊዊ ተባሂለ ስለእትፍለጥ ሰሙን ክንመሃሃር ኢና፡፡

“ብርሃንካን ሐቅኻን ልአኽ ይምርሑኒ ካዓ ናብ ቅዱስ እምባኻን መሕደሪኻን ድማ ይውሰዱኒ።” መዝ.43:3

ዲ/ን ፅጋቡ ወልዱ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታሕሳስ 14፣ 2006 ዓ.ም. ግእዝ)፡- በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን!!!
መእተዊ
 በቋንቋ ቤተክርስቲያን ወይም ብናይ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ቅድሚ በዓል ልደት ዘለዋ ሠለስተ ሰናብቲ፡- ስብከት፣ ብርሃንን ኖላዊን ብምባል ይፍለጣ፡፡ ቅድስቲ ቤተክርስቲያ ነገር ኩሉ ብግዚኡ አዝዩ ግሩም ገይሩ ንዝፈጠረ ኣምላክ ምስጋናአ ብዘመናት ከፋፊላ ምቕራብ ባህሪአ እዩ /መክ 3፣11/፡፡ ሕድሕድ ሰንበት ነናይ ባዕሉ ትምህርቲ ዝሐዘ እዩ፡፡ ካብተን ሠለስተ ሰናብቲ እተን ናይ መጨረሽታ ክልተ ማለት እውን ብርሃንን ኖላዊን እግዚአብሔር ብዝፈቐዶ መጠን ክንመሃሃር ኢና፡፡

Thursday, January 2, 2014

ነቢዩ ሚልክያስ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፳፬ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡-በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
“ሚልክያስ” ማለት “መልአክ፣ ሐዋርያ፣ መልእክተኛ” ማለት ነው፡፡ ጥር ፰ ቀን የሚነበበው ስንክሳር እንደሚያስረዳው ነቢዩ ሚልክያስ የተወለደው ሕዝቡ ከፄዋዌ (ከምርኮ) ከተመለሱ በኋላ ነው፡፡ ከሕፃንነቱ አንሥቶም የእግዚአብሔርን መንገድ የሚወድ ነበር፡፡ ሕዝቡም ይኽን አካኼዱን አይተው እጅግ ያከብሩት ነበር፡፡ ይኽን መልካምነቱንም አይተው “ከእግዚአብሔር የተላከ ነው” ሲሉ ስሙን ሚልክያስ ብለው ጠሩት፡፡

ነቢዩ ዘካርያስ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፳፫ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡-በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
“ዘካርያስ” ማለት “ዝኩር፣ ዝክረ እግዚአብሔር - እግዚአብሔር ያስታውሳል” ማለት ነው፡፡ ይኸውም በምርኮ የነበሩትን አይሁድ እግዚአብሔር እንዳሰባቸው የሚያስገነዝብ ነው፡፡ በምስጢራዊ መልኩ ግን እግዚአብሔር ኹል ጊዜ በእኛ ውስጥ ያለችውን ቤተ መቅደስ (ነፍሳችንን) እንድናንፃት እንደሚያሳስበን፣ በመንፈሳዊ ተጋድሎአችን ኹሉ እንደሚረዳን የሚያስገነዝብ ነው፡፡

ነቢዩ ሐጌ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፳፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡-በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 ሐጌ ማለት በዓል፣ ደስታ ማለት ነው፡፡ የስሙ ትርጓሜ ሕዝቡ ከምርኮ የሚመለሱ ስለኾነ ይኽን ደስታ የሚያስረዳ ነው፡፡
 በብሉይ ኪዳን በመጨረሻ የምናገኛቸው ሦስቱን መጻሕፍት ማለትም ትንቢተ ሐጌ፣ ትንቢተ ዘካርያስና ትንቢተ ሚልክያስ ከምርኮ በኋላ ስላለው ጊዜ እንዲኹም አይሁድ ከምርኮ እንዴት ወደ አገራቸው እንደተመለሱ የሚያስረዱ ናቸው፡፡ በዚያ አንጻር ግን ደቂቀ አዳም ከዲያብሎስ ምርኮ እንደምን ወደ እግዚአብሔር እንደተመለሱ የሚያረዱ ናቸው፡፡

ነቢዩ ሶፎንያስ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፳፩ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡-በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 ሶፎንያስ ማለት “እግዚአብሔር ይሰውራል፣ እግዚአብሔር ይጠብቃል፣ እግዚአብሔር ይከልላል” ማለት ነው፡፡ “እናንተ ፍርዱን የጠበቃችሁ የምድር ትሑታን ኹሉ እግዚአብሔርን ፈልጉ፤ ትሕትናንም ፈልጉ፤ ምናልባት በእግዚአብሔር ቊጣ ቀን ትሰወሩ ይኾናል” እንዲል /፪፡፫/፡፡

ነቢዩ ዕንባቆም

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፲፰ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡-በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ዕንባቆም ማለት ማቀፍ ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔርን በጸሎት አቅፎታልና እንዲኽ ተብሏል፡፡ ሊቃውንት እንደሚመሰክሩት ነቢዩ ዕንባቆም ያላ ገባ ድንግል ሲኾን የቤተ መቅደስ ዘማሪ ነበር /ዕን.፫፡፩/፡፡

FeedBurner FeedCount