Showing posts with label ልዩ ልዩ. Show all posts
Showing posts with label ልዩ ልዩ. Show all posts

Tuesday, April 8, 2014

ኒቆዲሞስ ዘቀዳሚት ሰንበት (ሆሳዕና)



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 3 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በአብና በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም፣ አንድ የናዝራውያን አምላክ፣ የማይለወጥ የሃይማኖት ምሰሶ፣ የማይፍገመገም የመርከባችን አለቃ፣ የማይጨልም የፋናችን ብርሃን፣ ከዘመናት በፊት በሕልውና አንድ የሆነ፣ በስምና በሥልጣን የሠለጠነ፣ የመለኮቱ አንድነት የማይለወጥ፣ የመንግሥቱ ስፋት የማይወሰን፣ የብልጥግናው ክብደት የማይለካ እርሱ በሰላም ይጠብቀን::

ኒቆዲሞስ ዘዓርብ (ሆሳዕና)



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 2 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በአንድነት በሚመሰገን፣ በአንድነትም በሚለመን፣ በአንድነት በሚሰበክ፣ አንደበት ሁሉ የሚገዛለት፣ ጉልበትም ሁሉ የሚሰግድለት፣ ምሥጉን አምላክ በሆነ በእግዚአብሔር ስም፣ በመጽሐፍ ራስ ሁሉ ላይ በጥበብ ቁጥር በእርሱ ስምና በመስቀሉ ምልክት በማማተብ ሰላምታ ይድረሳችሁ:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

ኒቆዲሞስ ዘሐሙስ (ሆሳዕና)



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 1 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ዙፋኑን በሚንቦገቦግ የእሳት ሰረገላ ላይ ያደረገ፣ በእሳት መጋረጃዎች የሚሰወር፣ በምሥጋናም መብረቅ የሚጋረድ፣ በኪሩቤል የሚመሰገን፣ በሱራፌልም የሚወደስ እስራኤል ያመሰገኑት አንድ አምላክ በሥልጣንና በቻይነት የሰለጠነ በሆነ በእግዚአብሔር ስም ሰላም ይሁንላችሁ:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

ኒቆዲሞስ ዘረቡዕ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 30 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 የሕልውናው መጀመሪያ ከመቼ ጊዜ ጀምሮ ነው የማይባል፣ ስለመጨረሻውም እስከመቼ ሁሉን አሳልፎ ይኖራል የማይባል፣ ከኪሩቤልና ከሱራፌል አንደበት ለእርሱ ምሥጋና ይሁን:: ለእርሱም መስቀልን በማመን እየተመኩ ራሳቸውንም በወንጌል ቀንበር እያስገዙ በቤተመቅደስ እና በመገናኛው ድንኳን ከሚሰበሰቡ ከምዕመናን ሥግደት የሚገባው የሰላም አምላክ ሰላሙን ይስጣችሁ:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

Monday, April 7, 2014

ኒቆዲሞስ ዘሠሉስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 29 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 የኦሪት ሰንኮፍን ከእኛ ያራቅህልን፣ በሚደነቅ አጠራር ከጨለማ ጠርተህ የዳግም ልደትን የሠጠኸን፣ ሰውነታችን ሳይሆን ነፍሳችን የምትጠራበትን ሕጽበት ምሥጢር የገለጥክልን፣ በሌሊት ጨለማ ሕይወታችን ወደ አንተ እንገሰግሳለን፤ አንተም የጽድቅን የእውነትን ነገር ትገልጥልናለህ:: ከዚያም እውነትህን መመስከር እንጀምራለን:: በመጨረሻም ማንም በሌለበት ወቅት እንኳን ከመስቀልህ ስር ቅዱስ ሥጋህን እንገንዝ ዘንድ እንደ ኒቆዲሞስ ያለፍርሃት በጽድቅና በእውነት እንኖራለን:: ምክንያቱም በአንተ መኖር ያለውን ሰላም ከአይሁድ ተለይተን አይተናልና:: ይህ ሰላምህ ሁልጊዜ አብሮን ይኖር ዘንድ ፈቃድህ ይሁን::

ኒቆዲሞስ ዘሠኑይ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 29 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ሰው በመሆናችን ልንሸከመው የማንችለውን ፍቅር ሰጠኸን፤ በጨለማ ሆነን አንተን ስንናፍቅ የማይጨልም ብርሃንን በሕይወታችን አበራህልን፤ የልባችንን ፍሬ መራራነት ታገስከን፤ የማስመሰላችንን ድራማ ቸል አልክልን፤ ስምህን ባጎደፍነው መጠን ሳይሆን በማይለካው ፍቅርህ ንጽሕናን አለበስከን፤ ፍቅርና ሰላም የለም ብለን ተስፋ በቆረጥን ጊዜ ይህ ነው በማይባል ሰዓት ደርሰህ እኛ የምንገረምበት እኛነት አደልከን፤ ሰላምን አጎናጸፍከን፤ በዚህ ሰላም ለሁላችሁ ሰላም ይሁን::

FeedBurner FeedCount