Wednesday, December 11, 2013

ነገረ ማርያም - ክፍል ፫ (የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ መግባት)



በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲሳት መምህር

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፫ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 ቅድስት ድንግል ማርያምም እስከ ሦስት ዓመት ድረስ በእናት በአባቷ ቤት ውስጥ ኖራለች፤ ይኽነን በእናት በአባቷ ቤት የነበራትን አስተዳደግ “Protoevangelium of James” (ፕሮቶቫንጊሊዩም ኦፍ ጀምስ) በሚለው ጥንታዊዉ መጽሐፍ ሲገልጽ (ሕፃኗም ከቀን ወደ ቀን በኀይልና በብርታት እያደገች ኼደች፤ የስድስት ወር ልጅ በኾነች ጊዜ እናቷ መቆም ትችል እንደኾነ ለማየት መሬት ላይ አቆመቻት፤ ርሷም ሰባት ርምጃ ተራምዳ ወደእናቷ ዕቅፍ ውስጥ ገባች፤ እናቷም እንዲኽ አለቻትወደ ጌታ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አስክወስድሽ ድረስ በራስች እንዳትራመጂ አለቻትና በመኝታ ቤቷ ውስጥ ውስጥ የቅድስና ስፍራ አበጀችላትአንድ ዓመት በኾናት ጊዜም ኢያቄም ታላቅ ግብዣ አድርጎ ካህናቱን፣ ጸሐፈትን፣ ታላቆችንና ሕዝብን ጠራ፤ ከዚያም ኢያቄም ልጁን ወደ ካህናቱ አቀረባት እነርሱምአባታችን እግዚአብሔር ሆይ ይኽቺን ልጅ ባርካት በትውልድ ኹሉ የሚጠራ ማብቂያ የሌለው ስምን ስጣት እያሉ ባረኳት፤ ሕዝቡም ኹሉይደረግ ይኹን ይጽና አሜንአሉ፤ ከዚያም ወደ ሊቀ ካህናቱ ወሰዳት ርሱምልዑል እግዚአብሔር ሆይ ይኽቺን ልጅ ተመልከት ለዘላለም በሚኖር በፍጹም በረከትም ባርካትበማለት ባረካት፤ ሐናም ይዛት ወደ ተቀደሰው የማደሪያዋ ክፍል በመውሰድ ጡትን ሰጠቻት…) ይላል፡፡

ነገረ ማርያም - ክፍል ፪ (የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የትውልድ ሀረጓ የተቀደሰ ታሪክ)



መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲሳት መምህር

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት እንዳስተማሩትና እንደጻፉት በእናቷ በሐና በኩል ያሉ የእመቤታችን ቅድመ አያቶቿ ጴጥሪቃ ቴክታ ሲባሉወኮኑ ክልኤሆሙ ጻድቃን ወፈራህያነ እግዚአብሔር ወይትአመንዎ ለአምላኮሙ በጥቡዕ ልብ እንበለ ኑፋቄይላል (ኹለቱም ሰዎች ደጋጐችና እግዚአብሔርን የሚፈሩ ያለምንም መጠራጠር በፍጹም ልቡናቸው በአምላካቸው የሚተማመኑ ነበሩ) እነሱም በጊዜው ይኽ ቀራችኊ የማይባሉ ባለጠጎች ነበሩ፤ ከሀብታቸው ብዛት የተነሣ ወርቁን ብሩን ንደ ዋንጫ እያሠሩ ከላሙ ከበሬው ቀንድ ይሰኩት ነበር፤ ይኽን ያኽል አቅርንተ ወርቅ፣ አቅርንተ ብሩር እየተባለ ይቈጠር ነበር የዕንቁ ጽዋ እንኳ ፸፣ ያኽል ነበራቸው፡፡

Tuesday, December 10, 2013

ነቢዩ ሕዝቅኤል

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ ታኅሳስ ፪ ቀን፥ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
“ሕዝቅኤል” ማለት “እግዚአብሔር ብርታትን ይሰጣል” ማለት ነው፡፡ ይኸውም በነቢይነት የተላከው በዘመኑ ወደ ነበሩ ዓመፀኞች ሰዎች፣ ፊታቸው የተጨማተረ ልባቸውም የደነደነ ልጆች ወደ እስራኤል ልጆች ስለ ነበረ እግዚአብሔር ብርታትን እንደሚሰጠው ሲያስረዳ ነው /ሕዝ.፪፡፫-፬/፡፡ ነቢዩ ሕዝቅኤል የካህኑ የቡዝ ልጅ ነው፡፡ እናቱም “ህሬ” እንደምትባል የቤተ ክርስቲያናችን ትውፊት ያስረዳል፡፡ የእስራኤል ካህን እንደ ነበር፤ ዳግመኛም ባለ ትዳር እንደ ነበር /ሕዝ.፰፡፩/ ተገልጧል፡፡

Sunday, December 8, 2013

ነቢዩ ኤርምያስ

ገ/እግዚአብሔር ኪደ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ኅዳር ፳፱፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
“ኤርምያስ” ማለት “እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ያደርጋል” ማለት ነው፡፡ ከአራቱ ዓበይት ነቢያት አንዱ ሲኾን መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን አባቱ “ኬልቅያስ” ይባላል፡፡ እናቱ ደግሞ “ማርታ” እንደምትባል የቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ትውፊት ያስረዳል፡፡ አገሩ በኢየሩሳሌም አቅራቢያ ካለው ከተማ ከ“ዓናቶት” ነው፤ ትውልዱም ከካህናት ወገን እንደነበረ ተጽፏል /ኤር.፩፡፩/፡፡

FeedBurner FeedCount