Sunday, March 16, 2014

መጻጉዕ ዘሠኑይ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 7 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ከባሕሪዩ በማይለወጥ በእግዚአብሔር አብ ስም፣ ከአባቱ በማይለይ በእግዚአብሔር ወልድ ስም፣ በአንደበቱ እስትንፋስ ነቢያትን እፍ ባለባቸው የጸጋውንም ወንጌል ይሰብኩ ዘንድ በተሰጠ ሰረገላዎችም ይሆኑት ዘንድ በእነርሱ ባደረ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ስም ሰላም ለሁላችሁ ይሁን::

መጻጉዕ ዘሰንበተ ክርስቲያን



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 7 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ሥጋችን በደዌ ተመትቶ መከራ በጸናብን ጊዜ፣ የኢዮብን ሥቃይ ማሰብ አቅቶን በደጅ ተንቀን በወደቅን ጊዜ፣ የምሬታችን ብዛት በአህዛብ ዘንድ ስድብ ሲሆንብን፣ በደጅህ ወድቀን የሚያነሳን ባጣን ጊዜ፣ የወለዱን እንኳን እኛን እስከመጨረሻው መሸከም ከብዷቸው በጣሉን ጊዜ፣ ሊሰሙን ያልወደዱ ነገስታት ሊጎበኙን ያልፈቀዱ ካሕናት በተሠበሰቡ ጊዜ፣ በቁስላችን ላይ ዘይትን በጥዝጣዜያችን ላይ መድኃኒትን የሚያፈሱልንን ባጣናቸው ጊዜ፣ አንተ ሳንጠራህ መጥተህ ሳንጠይቅህ ወደህ ሳንመካብህ መመኪያችን ሆነኸን ከሞት ጥላ በአባታዊ አጠራርህ ልጆቼ ብለህ ጠርተህልጆቼ መዳን ትወዳላችሁን?” ብለህ እንደ ታናሽ አስፈቅደህ መንጻትን በፈቀድን ጊዜ ከደዌያችን ሁሉ ጎንበስ ብለህ አጠብከን፡፡ ስለዚህም ማንም ሊሰጠን ያልፈቀደውን ሰላም ይልቁንም ማንም የሌለውን ሰላም ሰጠኸን:: በዚህ ሰላም ለሁላችሁ ሰላም ይሁንላችሁ!

Friday, March 14, 2014

ምኩራብ ዘቀዳሚት ሰንበት



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 5 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ሰማይን እንደ ድንኳን በዘረጋው፣ ምድርን በውኆች ላይ ባጸናት፣ ፀሐይንም መላእክትንም በሚመግባቸው፣ ከዋክብትንም እየመራ በነፋስ ሰረገላ በሚያመላልሰው፣ የወንጌልን ወተት ከኦሪት ወለላ ጋር ባጣፈጠ፣ የነቢያት ትንቢት ሽቶንም ከሐዋርያት የሃይማኖት ዘይት ጋር ባዋሐደ፣ በእግዚአብሔር ስም ሰላም ይሁንላችሁ:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

Thursday, March 13, 2014

ምኩራብ ዘዓርብ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 4 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

 እስከሞት ድረስ በወደደን፣ ስለፍቅር በሞተልን፣ በዚያች ቀን በቀኙ ባለው በኩል፣ ዛሬ ከእኔ ጋር ናችሁ ባለን፣ የእርሱን የምሕረት ቃል ከመስማት የበለጠ ደስታ በሌለን፣ በ30 ዘመን ፍቅሩ የሺህ ዘመን ኃጢአታችንን በደመሰሰልን፣ የምሕረቱን ጥልቅነት በሰውኛ ቋንቋችን ልንገጸው በማንችለው፣ በመስቀሉ ደም ቤዛችን ነፃነትና ሰላምን ባጎናጸፈን ሰላም ለእናንተ ይሁን!!

FeedBurner FeedCount