Thursday, March 27, 2014

ደብረዘይት ዘዓርብ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 18 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ሹመት የእርሱ በሆነ፣ መላእክቱን ለምስጋና በሚያሰልፍ፣ የነፍስ ረቂቅነት ግዙፉ በሆነ፣ ልባችንና ኩላሊታችን በሚታወቅበት፣ ዳግም ለሰው ልጆች የንስሃ ጊዜን በሚሠጥ፣ በደረቀ ሕይወት ዝናሙን በሚያዘንም፣ እውነተኛ የጽድቅ ጎዳና በሆነው በክርስቶስ ስም ሰላም ይሁንልን::

Wednesday, March 26, 2014

ደብረዘይት ዘሐሙስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 17 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ጥንት በሌለው፣ ለፊተኛው ፍጻሜ በሌለው፣ አስቀድሞ በነበረ፣ አሳልፎም በሚኖር የእርሱን እስትንፋስ እፍ ብሎ ሕይወት በሰጠን፣ የእርሱን ደም አፍስሶ ዳግም ሰው ባደረገን በልዑል እግዚአብሔር ወልድ ስም ሰላም ይሁንላችሁ::

Tuesday, March 25, 2014

ደብረዘይት ዘረቡዕ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 16 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
                 
 ከሦስትነቱ በማይነጠል፣ የሞቱ በሚነሱም ጊዜ ዳግመኛ ወደ ሥጋ አዳራሽ በሚመልሳት፣ የፀሐይና ጨረቃን አካሄድ ወደ ምዕራብ በሚመልስ፣ የወይራውን ዛፍ በሚነቅለው፣ የተቀጠቀጠውንም ሸምበቆ በሚያጸናው፣ በውጪ ያለውን በሚያስባ፣ በውስጥም ያለውን በሚያስወጣ፣ በእግዚአብሔር ስም በሁሉ ላይ የሠለጠነ ነውና ለእርሱ ምሥጋና ለእናንተም ሠላም ይሁን::

Monday, March 24, 2014

ደብረዘይት ዘሠሉስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 15 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በደሙ ፈሳሽነት በተሰቀለው መስቀል ባርኮ ድኅነትን በሰጠን፣ የአባቴ ቡሩካን ሊለን በታመነ፣ ከሚመጣው የልቅሶ ሕይወት እንወጣ ዘንድ በፍቅሩ በጠራን፣ በክርስቶስ ስም ሰላም ለእናንተ ይሁን::

 ወአንሰ በብዝኀ ምሕረትከ ዕበውዕ ቤተከእኔ በምሕረትህ ብዛት ወደ ቤትህ እገባለሁ፤ አንተን በመፍራት በመቅደስህ ፊት እሰግዳለሁ፤ አቤቱ በጽድቅህ ምራኝ::” ፍጹም ወደ ሆነችው ቤተክርስቲያን በሌሊት አንቅተህ ጠራኸን:: ነገር ግን እንገባ ዘንድ የተገባን አይደለንም፤ የአንተ ቸርነት ለሁሉ የተገባን፣ የአንተ ጸጋ ለሁሉ የተጠራን ያደርገናል እንጂ::

FeedBurner FeedCount