Wednesday, October 15, 2014

ለይሖዋ ምስክሮች ኑፋቄ የተሰጠ ምላሽ (ክፍል ኹለት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 5 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ምስጢረ ሥላሴ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት ነው!!!

 የምስጢረ ሥላሴ ትምህርት እግዚአብሔር የገለጠው እውነት እንጂ የይሖዋ ምስክሮች እንደሚሉት ሰዋዊ ትምህርት አይደለም፡፡ ቃሉን በቀጥታ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንፈልገው ብሎ መጠየቅ ግን የዕውቀት ማነስ ነው፡፡ ምክንያቱም የሚፈለገው የትምህርቱ መኖር እንጂ የቃሉ መኖር አይደለምና፡፡ እንኳንስ ሥላሴ የሚለው ቃል ይቅርና መጽሐፍ ቅዱስ የሚል ቃል እንኳን በራሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አናገኘውም፡፡

Sunday, October 12, 2014

ስለ አዳምና ሔዋን (ለሕፃናት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 03 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
       
የእግዚአብሔር ልጆች እንደምን ሰነበታችኁ? ደኅና ናችኁ? ትምህርት እንዴት ነው? ጐበዞች፡፡

ባለፈው ጊዜ ስለ ምን እንደተማርን ታስታውሳላችኁ ልጆች? ጐበዞች፡፡ የተማማርነው ስለ ሥነ ፍጥረት ነው አይደል? እስኪ ካስታወሳችኁ አዳምና ሔዋን መቼ ተፈጠሩ ነበር ያልነው? ጐበዞች፡፡ ልክ ናችኁ፡፡ ዓርብ ነበር የተፈጠሩት፡፡ ዛሬ ደግሞ ስለ አዳምና ስለ ሔዋን ታሪክ እነግራችኋለኁ፡፡ እናንተም ለመስማት ዝግጁ ናችኁ አይደል? ጐበዞች፡፡ 

Friday, October 10, 2014

ማኅሌተ ጽጌ፤ ምንጩ ትርጉሙና መልእክቱ (የመጨረሻው ክፍል)



በዲ/ ያረጋል አበጋዝ

 
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 30 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡


የቀጠለ…

4.4.
ማዕረረ ትንቢት ማርያም ዘመነ ጽጌ እንግዳ  
ወዘመነ ፍሬ ጽጋብ ዘዓመተ ረኃብ ፍዳ
ብኪ ተአምረ ዘይቤ ኢዩኤል ነቢየ ኤልዳ
ያንጸፈጽፍ እምአድባሪሁ ወእም አውግሪሁ ለይሁዳ
ፀቃውዓ መዓር ጥዑም ወሃሊብ ፀዓዳ»
ትርጉም
«
በመከር ጊዜ አበባ በአበባ ጊዜ ደግሞ መከር አዝመራ ማጨድና መሰብሰብ የለም፡፡ ምክንያቱም ጊዜያቸው የተለያየ ስለሆነ፡፡ ለምሳሌ በመስከረም ወር የአበባ ጊዜ በመሆኑ አዝመራ መሰብሰብ የለም፡፡»

Wednesday, October 8, 2014

ማኅሌተ ጽጌ፤ ምንጩ ትርጉሙና መልእክቱ (ክፍል ሦስት)



በዲ/ ያረጋል አበጋዝ

 
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 28 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡


የቀጠለ…


4. ምሥጢር
በዚህ ርዕሰ ጉዳይ የምናየው በብሉይና በሐዲስ የተነገረውን እያመሰጠረ፣ በብዙ አምሳልና ትንቢት ይነገር የነበረውን የአምላክን ከድንግል መወለድ፣ ትንቢቱን ከፍጻሜው ጋር እያዛመደ የሚናገረውን ነው፡፡ ከዚህም ውስጥ የተወሰኑትን እናያለን፡፡

FeedBurner FeedCount