Monday, February 22, 2016

ትንቢተ ዮናስ - ክፍል ሦስት



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 15 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ምዕራፍ ሦስት

ዓሣው ዮናስን በአንጻረ ነነዌ ተፋው፡፡ እግዚአብሔርም ልክ እንደ መጀመርያው፡- “ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፤ እኔ ከዚህ ቀደም አስተምር ብዬ እንደነገርኩህ አስተምራቸውአለው፡፡ ዮናስም መጀመርያ እንዳደረገው ከጌታ ፊት ለመሸሽ አልሞከረም፡፡ እግዚአብሔር እንዳዘዘው ተነሥቶ ሄደ እንጂ፡፡ ተወዳጆች ሆይ! እስኪ የእግዚአብሔርን ፍቅር ቆም ብለን እናሰላስለው፡፡ ዮናስ ለወገኖቹ ለእስራኤል አዝኖ አልታዘዝ ብሎ ነበር፡፡ ባለመታዘዙ ምክንያትም ወደ ሌላ ኃጢአት ገብቶ ነበር፡፡ እግዚአብሔር ግን አሁንም ይወዷል፡፡ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማሌላ ነቢይ ልላክአላለም፤ከእንግዲህ ወዲህ ዮናስን አልፈልገውምአላለም፡፡ እግዚአብሔር ዮናስን በቃል እንኳ የገሰጸው አይደለም፡፡ ዳግመኛምዮናስ ሆይ! ትእዛዜን ተላልፈህ የሸሸኸው ስለምንድነው?” አላለውም፡፡ በተግባር የደረሰበት ኹሉ በቂ ነውና፡፡ በመኾኑም አሁን ተጨማሪ የቃል ተግሳጽ አላስፈለገውም፡፡ ዳግመኛ በቃላት ቢገስጸው ዮናስ ምን ያክል ስሜቱ ሊጐዳ እንደሚችል ሰው ወዳጁ ጌታ ያውቃልና፡፡ እግዚአብሔር ስሜታችንን ምን ሊጐዳው እንደሚችል ጠንቅቆ ያውቃል፤ በመኾኑም ይጠነቀቅልናል፡፡ ስሕተታችን ምን እንደኾነ በራሳችን አውቀን እንድንመለስ ኹኔታዎችን ያመቻችልናል እንጂ እየመላለሰ እንደ ሰው አይነዘንዘንም፡፡ ስሙ የተመሰገነ ይኹን! ወገኖቼ! ገና ስንጀምር እንደተናገርነው ይህቺ ከተማ ድሀ የሚበደልባት ጣዖት የሚመለክባት የሞት ከተማ ናት፡፡ ክፋትዋ ጽርሐ አርያም የደረሰ ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን አሁንም ይወዳታል፡፡ እግዚአብሔር ግን አሁንም ያፈቅራታል፡፡ እግዚአብሔር የሚጠላው ፍጥረትስ ማን አለ? የቅዳሴ ማርያም ጸሐፊ አባ ሕርያቆስ እንደተናገረው እግዚአብሔር ያፈቅራል፤ እግዚአብሔር ባለሟል ያደርጋል፤ እግዚአብሔር ዝቅ ብሎ እንደ ሰው ያናግራል፡፡ መልካም ስላገኘብን አይደለም፤ ባሕርዪው ፍቅር ስለኾነ እንዲሁ ያፈቅናል እንጂ፡፡ እግዚአብሔር ኃጢአተኛውን ይፈልገዋል፡፡ እግዚአብሔር ደካማውን ይፈልገዋል፡፡ እርሱ የሚጠላው ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኛውን አይደለምና፡፡ እግዚአብሔር የሚጸየፈው የነነዌን ኃጢአት እንጂ የነነዌን ሰዎች አይደለም፡፡ እግዚአብሔር የሚጸየፈው እኛን አይደለም፤ ኃጢአታችንን እንጂ፡፡ አባት ልጁን እንዴት ይጠላል?

ትንቢተ ዮናስ - ክፍል ኹለት



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 14 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


ምዕራፍ ኹለት


ዮናስ ወደ ባሕሩ ተጣለ፡፡ ኾኖም ይሞት ዘንድ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነውና ይሞት ዘንድ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር የነነዌን ሰዎች እንዲያድናቸው ወዷልና ዮናስ የተጣለው እንዲሞት አይደለም፡፡ በሰዎች እይታ ዮናስ ለዚህ የተገባ አይደለም ሊባል ይችላል፡፡ በእግዚአብሔር እይታ ግን የተገባ ነው፡፡ አሁንም እግዚአብሔር ይወዷል፤ ልጄ ይሏል፤ የእኔ ነቢይ ብሎ ይጠራዋል፡፡ ምንም እንኳን ለወገኖቹ ለእስራኤል አዝኖ አልታዘዝ ቢልም፣ አለመታዘዙ ወደ ሌላ ኃጢአት እንዲገባ ቢያደርገውም አሁንም እግዚአብሔር ዮናስን ይፈልገዋል፡፡ ነነዌን ያድናታል፡፡ እግዚአብሔር ትዕግሥተኛ ነው፡፡ እንደ እኛ ለፍርድ አይቸኩልም፡፡ ለመቅጣት አይቸኩልም፡፡ በወደቁ ልጆቹ ፈጥኖ አይፈርድም፡፡ ለፍርድ የምንቸኩለው እኛ ነን፡፡ ከወደቁ ሰዎች ጋር ያለን ግንኝነት ፈጥነን የምናቋርጥ እኛ ነን፡፡ እርሱ እግዚአብሔር ግን እንዲህ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ጠባቂ ነው፡፡ በጣም ብዙ ጊዜ ይጠብቃል፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ በትዕግሥት የሚጠብቀን ባይኾን እስከ አሁን ማን ይቆይ ነበር? ማን ቀና ብሎ ይሄዳል? የቆየነው እንጀራ ብቻ በልተን አይደለም፤ መድኃኒት ውጠንም አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ስለጠበቀን እንጂ፡፡ ስንበድል ዕድሜ ለንስሐ ሰጥቶን እንጂ፡፡ ስንቶቻችን መርዝ በጥብጠናል? ስንቶቻችን ገመድ አንጠልጥለናል? ስንቶቻችን ስለት ስለናል? እግዚአብሔር ግን ከዚያ ጠበቀን፡፡ አሁንምልጄ! እወድሃለሁ፤ ልጄ! እወድሻለሁይለናል፡፡

FeedBurner FeedCount