Friday, March 21, 2014

ደብረዘይት ዘሰንበተ ክርስቲያን



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 12 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 እኛ ክርስቲያን እንባል ዘንድ፣ ከክርስቲያኖችም ጋር እንኖር ዘንድ፣ በዘመናችንም ሁሉ እንደኖሩት ሐዋርያት ትምህርት እንኖር ዘንድ፣ እንደ አባቶቻችን ሐዋርያት ክርስቲያን ሆነን በመቃብር ውስጥ ባንቀላፋንም በዚያ በደብረዘይት በምንነሳም ጊዜ ከእነርሱ ጋር በእነርሱ እቅፍ እንቀመጥ ዘንድ በአንተ ፍቅር ልንኖር ግድ ይለናል:: በማይለወጥ ፍቅሩ ሰላም ለእናንተ ይሁን::

መጻጉዕ ዘቀዳሚት ሰንበት



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 12 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በስሙ ስሙን አግኝታችሁ፣ በእርሱ የምትገቡ፣ ምርጦች ሆናችሁ የተጠራችሁ፣ የጨለማ ስራን አስወግዶ ወደሚደነቅ ብርሃን ያወጣችሁ፡፡ በይቅርታና በፍቅር ወደ እናንተ የመጣ ክርስቶስን ከላይ እንደ ልብስ ከውስጥ ደግሞ እንደ አካል የለበሳችሁት፣ ኃጢአትና ልምምዷን አሸንፎ በአባታዊ ፍቅር ልጅነትን ያደላችሁ ሁላችሁ በእርሱ በእግዚአብሔር ልጅ ሰላምታ ሰላም ይሁንላችሁ::

Thursday, March 20, 2014

መጻጉዕ ዘዓርብ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 11 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 እስከሞት ድረስ በወደደን፤ ስለፍቅር በሞተልን፤ በዚያች ቀን በቀኙ ባለው በኩልዛሬ ከእኔ ጋር ናችሁ” ባለን፤ የእርሱን የምሕረት ቃል ከመስማት የበለጠ ደስታ በሌለን፤ 30 ዘመን ፍቅሩ የሺህ ዘመን ኃጢአታችንን በደመሰሰልን፤ የምሕረቱን ጥልቅነት በሰውኛ ቋንቋችን ልንገልጸው በማንችለው፤ በመስቀሉ ደም ቤዛችን በሆነን፤ ነፃነትና ሰላምን ባጎናጸፈን ሰላም ለእናንተ ይሁን::

Wednesday, March 19, 2014

መጻጉዕ ዘሐሙስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 10 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ክርስቶስ አምላኬና ተስፋዬ ነው፤ እፀ መስቀሉም የሐይማኖቴ በትር ነው፤ የጎኑም መወጋት የጥምቀቴ ሻሻቴ፤ የግርፋቶቹም ደም የበለሳን ቅባቴ ነው:: ሐዋርያቱ በመንገዱ የሚመሩኝ ናቸው:: እመቤቴ ማርያም የመድኃኒቴ በር ናት፤ ክንፎቿ በብር የተሠሩ ጎኖቿም በወርቅ ሐመልማል የተሠሩ ነጭ ወፍ (መጽሐፈ ምስጢር):: በሰላማዊቷ ነጭ ወፍ ሰላምታ ሰላም ይሁንላችሁ::

FeedBurner FeedCount