Friday, June 15, 2012

ልዩ ፍርድ ቤት- በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ!!


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
  “የብዙዎቻችን ከንፈሮች ለሐሜት የተከፈቱ ናቸው፡፡ የራሳችንን ግንድ ትተንም ከሰዎች ጉድፍን ለማውጣት እንዳዳለን፡፡ በወንድሞቻችንም ላይ እንፈርዳለን፡፡ ተወዳጆች ሆይ! እንጠንቀቅ! የፍርድ ዙፋን ያለው ከእርሱ ጋር ብቻ ነውና የወልድን ሥልጣን እኛው አንያዘው፡፡
መፍረድ ትፈልጋላችሁን? እንግዲያስ ምንም የማያስወቅስና በጣም ብዙ ጥቅም ያለው የፍርድ ችሎት አለላችሁ፡፡ አጥብቃችሁ በራሳችሁ ላይ ለመፍረድ ተቀመጡ፡፡ አስቀድማችሁ በደላችሁን ከፊታችሁ በመዝገብ አስቀምጡት፤ የነፍሳችሁም ወንጀል በሙሉ መርምሩ፤ ተገቢውንም ፍርድ አስቀምጡና ነፍሳችሁንይህንና ያንን በደል ያደረግሺው ለምንድነው?በሏት፡፡ ከዚህ ፈቀቅ ብላ የሌሎችን ሰዎች ኃጢአት መፈለግ ከጀመረችየተከሰስሽበት ጉዳይ የእነዚያ አይደለም፣ አንቺም የመጣሽው ስለነዚያ ሰዎች ለመሟገት አይደለም፡፡ ስለምንድነው ክፋትን የሠራሽው? ስለምንስ ነው ያንንና ይህን ጥፋት ያጠፋሽው? የራስሽን ተናገሪ እንጂ ሌሎችን አትውቀሺበሏት፡፡ ሁል ጊዜም ይህን አስጨናቂ ፈተናን እንድትመልስ አቻኩሏት፡፡ ተሸማቅቃ ምንም የምትመልሰው ነገር ከሌላትም አስፈላጊውን ቅጣት (ቀኖና) ወሱንባት፡፡ ይህን ልዩ ፍርድቤት ሁል ጊዜ የምትቀመጡ ከሆነ የእሳት ሸሎቆው፣ መርዘኛው ትልና ሊመጣ ያለውን ስቃይ በአእምሮዋችሁ እንዲቀረፅ ይረዳችኋል፡፡

ሁልጊዜምእሱ ወደ እኔ መጥቶብኝ ነው፤ እሱ ሸውዶኝ ነው፤ እሱ ፈትኖኝ ነውእያለች ከዲያብሎስ ጐን እንድትሰለፍና ሐፍረት የለሽ ንግግሮችን እንድትናገር አትፍቀዱላት፡፡ ይልቁንምአንቺ ፍቃደኛ ባትሆኚ ነው እንጂ እነዚህ ሁሉ ካንቺ ጋራ ምንም ጉዳይ የላቸውምብላችሁ ንገሯት፡፡እኔ እኮ ሥጋ ለባሽ ነኝ፣ የምኖረውም በምድር ነውካለቻችሁምይህ ሁሉ ሰበብና ምክንያት ነው፡፡ ብዙዎች አንቺ የለበስሽውን ሥጋ

Wednesday, June 13, 2012

ይህ በእውነት ወደ ዓለም የሚመጣው ነቢይ ነው- የዮሐንስ ወንጌል የ27ኛ ሳምንት ጥናት (ዮሐ.6፡1-15)!!


          በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

 ተወዳጆች ሆይ! ከክፉዎች ጋር ክፉዎች አንሁን፡፡ ይልቁንም ክፋታቸው በእኛ ላይ ምንም ዓይነት ጕዳት ሊያመጣ እንደማይችል እንረዳ፡፡ አንድ የሚፈነዳ መሣርያ ድንጋይ ላይ ቢወረወር ተስፈንጥሮ ወደ ወረወረው ሰውዬ ይመለሳል፤ ይጐዳዋልም፤ ባስ ካለም ሕይወቱን ሊያሳጣው ይችላል፡፡ ምናልባት የተወረወረው መሣርያ ለስላሳ መሬት ላይ አርፎ ቢሆን ግን መሬቱ የመሣርያውን ግለት ስለሚያቀዘቅዘው ሰውዬውን ባልጐዳው ነበር፡፡ በእኛ ላይ ክፋትን የሚፈጽም ሰውም እንደዚሁ ነው፡፡ እኛ መልሰን ክፋት የምናደርግበት ከሆነ ክፋቱን ይበልጥ ይገፋበታል፤ እኛ ትዕግሥተኞችና ሰው ወዳዶች ብንሆን ግን ክፋቱን እንዲመለከት መስታወት ስለምንሆነው ከክፋቱ ይቀዘቅዛል፡፡ ይህን የምንለው ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ይልቁንም ጸሐፍትና ፈሪሳውያን ጌታችን ከዮሐንስ ይልቅ ደቀ መዛሙርት እንደሚያደርግ በሰሙ ጊዜ በእርሱ ላይ ክፋትን ለመፈጸም ወደ ቃና ዘገሊላ ስለሚሄዱ እንጂ፡፡ ሰው አፍቃሪው ጌታ ግን ይህን ክፋታቸው ስላወቀባቸው እንዳይገፉበትና ራሳቸውን የበለጠ እንዳይጐዱ ስለወደደ እነርሱ ወዳሉበት ወደ ቃና ዘገሊላ አልሄደም፡፡  ይልቁንም “የጥብርያዶስ ባሕር ወደሆነው ወደ ገሊላ ባሕር ማዶ ተሻገረ” እንጂ /ቁ.1/፡፡ ሲሄድም “በበሽተኞች ያደረገውን ምልክቶች አይተው ብዙ ሰዎች ተከተሉት” /ቁ.2፣ ምዕ.5፡9/። እነዚህ ሰዎች ሐዋርያው “በልሳን መናገር (በአጠቃላይ ተአምራትን ማድረግ!) ለማያምኑ ምልክት ነው እንጂ ለሚያምኑ አይደለም” እንዳለው ከጌታችን ትምህርት ይልቅ ተአምራቱ ይማርካቸው ነበር፡፡ /1ቆሮ.14፡22፣ Saint John Chrysostom, Homilies on St. John, Hom: 42:1/።
 ከዚህ በኋላ “አስተምራችሁ ገስጻችሁ፣ መክራችሁ ዘክራችሁ የራሳችሁ የሆነ የጽሞና ጊዜ ያስፈልጋችኋል፤ ከጥብብ ምንጭ ከእግዚአብሔር ጋር የምትገናኙበት ልዩ ጊዜ ሊኖራችሁ ይገባል፤ እንዳትታበዩ ሥጋችሁን የምትጐስሙበት ትሕርምት፣ ጾም ጸሎት ያስፈልጋችኋል” ሲልወደ ተራራ ወጣና በዚያ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተቀመጠ” /ቁ.3/።  ይህም ሲሆን የአይሁድ በዓልም ፋሲካ ቀርቦ ነበር” /ቁ.4/፡፡ ሆኖም ግን ጌታችን ወደዚሁ ገቢረ በዓል አይሄድም፡፡ አስቀድመን እንደተነጋገርነው በቤተ መቅደሱም ያሉት ጸሐፍትና ፈሪሳውያን አብዝተው ሊገድሉት ይፈልጋሉና፡፡ ስለዚህ ፈርቶ ሳይሆን ጊዜው ስላልደረሰ፣ አንድም ለክርስቲያኖች መሸሽ ኃጢአት አለመሆኑን ለማሳየት፣ አንድም እነዚህ ሰዎች እርሱን የጐዱ መስሎዋቸው ራሳቸውን እንዳይጐዱ፣ አንድም ነፍሱ በዓላቶቻቸውን እንደጠላች ደግሞም እንዳለፉ ለማሳየት ወደ ገቢረ በዓላቸው አይሄድም /ኢሳ.1፡14፣ Saint John Chrysostom, Ibid /፡፡

    ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በተራራው በተቀመጠ ጊዜ፣ ከልጆቹ ጋር መነጋገር በጀመረ ጊዜ ዓይኖቹን አራምዶ አየ፤ ብዙ ሕዝብም ወደ እርሱ ሲመጡ ተመለከተና አዘነላቸው /ቁ.5፣ ማቴ.14፡6/፡፡ አቤት ፍቅር! አቤት ቸርነት! አቤት ርኅራኄ! ወንድሞቼ እስኪ የጌታችንን የፍቅር ፊት በኅሊናችሁ ሣሉት! እስኪ የርኅራኄና ሰው ወዳዱ ፊቱን በልቡናችሁ ቅረጹት፡፡ አያችሁ?! ጌታ እንዲህ ይወደናል! አባታችን እንዲህ ይሳሳልናል! ወዮ አባት ሆይ ስላፈቀርከን እናመሰግንሃለን!!

   ከዚህ በኋላ ኅብስቱን አበርክቶ ሊሰጣቸው እንደሚችል ኃይልና ሥልጣን እንዳለው ቢያውቅም ደቀ መዛሙርቱ ገና በእምነት ያልጠነከሩ ስለነበሩ እምነታቸው ይጨምር ዘንድ በፊልጶስ በኵል፡-“ለእኒህ ሰዎች የምንመግባቸውን እንጀራ ከወዴት እንገዛለን?” አላቸው። ይህም እግዚአብሔር ሙሴን ለማሳመን ያደረገውን ተአምር ያስታውሰናል፡፡ ሙሴ እስራኤላውያንን ከፎርዖን አገዛዝ እንዲያላቅቃቸው በእግዚአብሔር ሲታዘዝ

Saturday, June 9, 2012

.........ታጠቅ...!...


                            በልዑል ገ/እግዚአብሔር!

'ድው...ድው...ድው...'
ነጋሪት ተጎስሟል
መለከት ተነፍቷል

ጠላት ሸምቆ
ትጥቁን ታጥቆ
በጦር አውድማ ሊወጋህ
ለስቃይ ሊጥልህ ሊያደማህ
ወግቶ አድምቶ ሊገልህ
ከምድረ ገጽ ሊያጠፋህ

እሳት ለብሶ
እሳት ጎርሶ
በሜዳ ላይ ቆሟል
ሊበላህ ጎምዥቷል

'
ድው...ድው...ድው...'
ነጋሪት ተጎስሟል
መለከት ተነፍቷል

ታጠቅ:-
ጦር ምዝራቅህን ሰብቅ
ጠመንጃ ነፍጥህን ታጠቅ
ሰይፍ ሜሎስህን መርቅ

ትጥቅህ ኃይለኛው
የአንበሳ ክንድ ነው
ያደቃል ያበራያል
ያጠፋል ያወድማል

አይዞህ:-
አትፍራው በለው
ወደ ኃላ አባረው
ሲፎክር ሲሸልል

Friday, June 8, 2012

ከዮሐንስ ምስክር የሚበልጥ ምስክር አለኝ- የዮሐንስ ወንጌል የ26ኛ ሳምንት ጥናት (ዮሐ.5፡30-ፍጻሜ)!


     በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

 አንድ ምንም እውቀቱና ልምዱ የሌለው ሰው ዝም ብሎ መሬት ስለ ቆፈረ ብቻ ወርቅ አያገኝም፡፡ ከዚያ ይልቅ ምንም ረብሕና ጥቅም የሌለውን ድካም ያተርፋል እንጂ፡፡ ባስ ካለም የቆፈረው ጉድጓድ ተደርምሶበት ሕይወቱን ሊያጣ ይችላል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንዴት እንደሚነበብና እንዴት መረዳት እንዳለበት ያለወቀ ሰውም ይህን ሰው ይመስላል፡፡ ይህንን የምንለው ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ይልቁንም ቀጥለን የምንመለከተው ቃል በቀላሉ ሊረዱት የማይችሉና ሰም ለበስ ወርቅ ስለሆነ እንጂ፡፡ ጌታችን “እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ እንደ ሰማሁ እፈርዳለሁ ፍርዴም ቅን ነው፥ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና።  እኔ ስለ እኔ ስለ ራሴ ብመሰክር ምስክሬ እውነት አይደለም” ስላለ ብቻ እንዲሁ ጥሬ ንባቡን በመያዝ ብዙ ሰዎች ይደናበራሉ /ቁ.30-31/፤ እውነት የሆነው “ክርስቶስ ስለ ራሱ የመሰከረው ምስክርነት እውነት አይደለም” ለማለት ይደፍራሉ፡፡ ሆኖም ግን ጌታችን ይህንን ሲል እነርሱ እንደሚሉት ማለቱ አልነበረም፡፡ አይሁድ “እግዚአብሔር አባቴ ነው፤ ከአባቴ ጋር የተስተካከልኩ ነኝ፤ አባቴ እስከ ዛሬ እንደሚሠራ እኔም በአንድ ፈቃዲት በአንዲት ሥልጣን እንዲህ አደርጋለሁ” ቢላቸው “አንተ ስለ ራስህ ትመሰክራለህ፤ ምስክርነትህ እውነት አይደለም፡፡ ስለዚህም አናምንህም” /ዮሐ.8፡13/ ስለሚሉትና ሊገድሉት ስለሚፈልጉ፡- “እኔ ምንም ምን ከራሴ ብቻ አንቅቼ አላስተምርም፤ በህልውና እንደሰማሁ የሰማሁትን አስተምራለሁ እንጂ፡፡ ትምህርቴም እውነት ነው፤ የእኔ ፈቃድ ከአባቴ ፈቃድ ልዩ ሆኖ የእኔ ፈቃድ ብቻ ሊደረግ አልወድም፤ ወልድ ያልወደደው አብም አይወደውም” ነው የሚላቸው /ወንጌል ቅዱስ አንድምታ ገጽ 481/፡፡

   ሰው ወዳጁ ጌታ ንግግሩን በዚህ አያቆምም፤ ይልቁንም እንዲህ ብሎ ይቀጥላል እንጂ፡- “የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ስላልሁ፣ አብ ልኮ ያዋሐደኝ አምላክ ነኝ ብላችሁ እናንተ ግን ትሳደባለህ ትሉኛላችሁ፡፡ ሆኖም እኔ የአባቴን ሥራ ባላደርግ፣ የአምላክነትን ሥራ ባላደርግ አትመኑኝ፤ ምስክርነቴንም አትቀበሉ፤ ባደርገው ግን እኔን እንኳ ባታምኑ አብ በእኔ ህልው እንደሆነ እኔም በአብ ህልው እንደሆንሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ ሥራውን እመኑ”/ዮሐ.10፡36/፤ አብ ሙታንን እንደሚያነሣ ሕይወትም እንደሚሰጣቸው እኔም ለምወዳቸው ለሚያምኑብኝ ሕይወትን የመስጠት ኃይልና ሥልጣን እንዳለኝ እመኑ፡፡ አንተ ስለራስህ የምትመሰክረው ምስክርነት አንቀበልም ብትሉ እንኳን አብ ስለ እኔ የሚመሰክረውን ለመቀበል አትቸገሩ፤ የማደርገውን ሥራ አይታችሁ እመኑ፡፡ እናንተ ወደ ዮሐንስ ልካችሁ አልነበረምን? እርሱስ፡-እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔረ በግ ብሎ እውነት ነግሯችሁ አልነበረምን? /ዮሐ.1፡29/:: እንግዲያውስ ዮሐንስ የመሰከረላችሁ ምስክርነት እመኑ፡፡ ስለ ራስህ ምን ትላለህ? ሳይሆን ስለ ክርስቶስ ምን ትላለህ? ብላችሁ ጠይቁትና እመኑ፡፡ እናንተ እንድትድኑ ይህን እላለሁ እንጂ እኔስ  ከሰው ምስክር አልቀበልም፡፡ እናንተ ትወዱት ስለ ነበረ እንደ ነብይም ታዩት ስለ ነበረ የእርሱን ትምህርት አድምጣችሁ በእኔ ታምኑ ዘንድ ትምህርቱን አስታወስኳችሁ እንጂ አምላክነቴን ለማረጋገጥስ የማደርገው ተአምራት ራሱ በቂ ነው /ቁ.34፣ Saint John Chrysostom  Homilies on ST. John, 41/፡፡

FeedBurner FeedCount