Tuesday, May 12, 2015

“ከካህናት ጋር አብሬ ስለማገለግል ንስሐ መግባት ከበደኝ፡፡ ምን ላድርግ?”



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ግንቦት 4 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ውድ መቅረዛውያን እንዴት አላችኁ? ዛሬም ከአንባብያን ከተላኩልኝ ጥያቄዎች መካከል አንዱን መርጬ በአበው ካህናት የተሰጠውን ምላሽ ይዤላችኁ ቀርቢያለኁ፡፡ ዛሬም መልሱን የሚሰጡን በምሥራቀ ፀሐይ ቀበና መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል እንዲኹም በታዕካ ነገሥት ባዕታ ለማርያም ገዳም የመጻሕፍተ ሐዲሳት የ5ኛ ዓመት ደቀ መዝሙርና የዘንድሮ ተመራቂ የኾኑት ቀሲስ ፋሲል ታደሰ ናቸው፡፡ ለአባታችን ተናጋሪ አንደበት ለእኛም ሰሚ እዝነ ልቡና ያድለን፡፡ አሜን!!!
ጥያቄ፡-  “ውድ መቅረዞች! እንዴት አላችኁ? የመቅረዝ አንባቢ ነኝ፡፡ ከምእመናን የምታስተናግዱት ጥያቄ በጣም ጥሩ ነው፡፡ እኔም ከንስሐ አባት ጋር የተያያዘ ጥያቄ አለኝ፡፡ እኔ በምኖርበት አከባቢ ከካህናት ጋር አብሮ የመሥራትና የመቀራረብ ነገር አለ፡፡ ይኽም ለእኔ ብቻ ሳይኾን የሀገሩ ጠባይ የፈጠረው ነው፡፡ እናማ ባለን ቅርርብ በቤተ ክርስቲያን ጕዳይ አለመግባባት ሲፈጠርም ኾነ በሌላ ጕዳይ በአካልም ኾነ በስልክ እንደ ልብ ስለምናወራ የሰው ስም እያነሣን ስናማ፣ ስናወግዝ አብረን ስለምንውል እንዴት መናዘዝ እችላለኁ?”
አንዳርግ ነኝ ከቺካጎ

Saturday, May 2, 2015

ለክርስትና ሃይማኖት ግድ ያለው ሰው ኹሉ ሊያነበው የሚገባ መጽሐፍ!



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 24 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተዘጋጀውና “መድሎተ ጽድቅ (የእውነት ሚዛን)” የተሰኘው ድንቅ መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ፡፡
ይኽ መጽሐፍ ራሳቸውን “ተሐድሶ” ብለው የሚጠሩት አካላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነትና ትምህርትን በተመለከተ በሐሰትና በስሕተት ላሠራጯቸው የስሕተት ትምህርቶች መልስ የሚሰጥ ድንቅ መጽሐፍ ሲኾን በአንጻሩም መጽሐፍ ቅዱሳዊና ሐዋርያዊ የኾነው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ትምህርት በጥልቀትና በስፋት የቀረበበት መጽሐፍ ነው፡፡ በውስጡም፡-

Thursday, April 30, 2015

ስለ ጌጠኛ ልብስ

በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 22 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ዕርቃናችንን የምንሸፍንበት ልብስ ብቻ ልንለብስ ይገባናል፡፡ ብዙ ወርቅን ብናደርግ ምንድነው ትርጉሙ? ብዙ ወርቅን ማድረግ በተውኔት ቤት ነው፤ ተዋንያን ብዙ ተመልካችን ለማግኘት ያደርጉታልና፡፡ ጌጠኛ ልብስ መልበስ የአመንዝራ ሴቶች ግብር ነው፤ ብዙ ወንዶች ይመለከቷቸው ዘንድ ይኽን ያደርጋሉና፡፡ እነዚኽን ማድረግ ልታይ ልታይ ለሚሉ ሰዎች ነው፡፡ እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት የምትሻ ሴት ግን ይኽን ጌጥ ማድረግ አትፈልግም፡፡ ራሷን የምታስጌጠው በሌላ መንገድ ነው፡፡ እናንተም ይኽን ጌጥ ማድረግ የምትፈልጉ ከኾነ ማድረግ ትችላላችኁ፡፡ ተውኔት ቤትን የምትሹ ከኾነም ወርቀ ዘቦአችኁን የምታደርጉበት ሌላ ተውኔት ቤት አለላችኁ፡፡ ያ ተውኔት ቤትስ ምንድነው? መንግሥተ ሰማያት ነው፡፡ ተመልካቾቹ ቅዱሳን መላእክት ናቸው፡፡ ይኽን የምናገረው በገዳም ለሚኖሩት መኖኮሳይያት ብቻ አይደለም፤ በማዕከለ ዓለም ለሚኖሩትም ኹሉ ጭምር እንጂ፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን በወልድ ውሉድ የተባለ ኹሉ የራሱ ተውኔት ቤት አለው፡፡ ስለዚኽ ተመልካቾቻችንን ደስ ለማሰኘት ራሳችንን ደኅና አድርገን እናጊጥ ብዬ እማልዳችኋለኁ፡፡ ለመድረኩ የሚመጥን ልብስን እንልበስ፡፡ እስኪ ንገሩኝ! አንዲት ሴሰኛ ሴት ተውኔት ለመሥራት ብላ ብዙ ወርቋን አወላልቃ፣ ቄንጠኛ መጎናጸፍያዋን ጥላ፣ በሳቅ በስላቅ ሳይኾን ቁም ነገርን ይዛ፣ ተርታ ልብስን ለብሳ ወደ መድረኩ ብትወጣና ሃይማኖታዊ ንግግርን ብትናገር፣ ስለ ንጽሕና ስለ ቅድስና ብትናገር፣ ሌላ ክፉ ንግግርም ባትጨምር በተውኔት ቤቱ የሞላው ሰው አይነሣምን? ተመልካቹ ኹሉ የሚበተን አይደለምን? ሰይጣን የሰበሰበው ተመልካቹ የማይፈልገውን ነገር ይዛ ስለ መጣች ኹሉም የሚሳለቅባትና እንደ ትልቅ አጀንዳ የሚወራላት አይደለምን? አንተም በብዙ ወርቅ፣ በጌጠኛ ልብስ ተሸላልመኽ ወደ መንግሥተ ሰማያት ብትገባ ቅዱሳን መላእክት አስወጥተው ይሰዱኻል፡፡ ምክንያቱም በመንግሥተ ሰማያት የሚያስፈልገው ልብስ እንደዚኽ ዓይነት አይደለም፤ ሌላ ነው እንጂ፡፡ “ርሱስ ምን ዓይነት ነው?” ትለኝ እንደኾነም “ነፍስን በትሩፋት ማስጌጥ ነው” ብዬ እመልስልኻለኁ፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ክቡር ዳዊት፡- “ልብሷ የወርቅ መጐናጸፍያ ነው” ያለውም ይኽንኑ ነው እንጂ በዚኽ ምድር የምንለብሰው ልብሳችንን ፀዓዳና አንጸባራቂ ስለ መኾን አይደለም /መዝ.45፡13/፡፡ ምክንያቱም “ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ኹሉ ክብሯ ነው” እንዳለ በዚያ (በመንግሥተ ሰማያት) መራሔ ተውኔቷ ርሷ ናት፡፡ እኅቴ ሆይ! ራስሽን መሸላለም ብትፈልጊ እንዲኽ አጊጪ፡፡ ከዚያም ከምረረ ገሃነም ትድኛለሽ፡፡ ባልሽንም ከማዘን ከመቆርቆር ትታደጊዋለሽ፡፡

Tuesday, April 28, 2015

የጉባኤ ጥሪ ከዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት

“ተዋሕዶ ሃይማኖታችን፣ ቤተ ክርስቲያን እናታችን” በማለታቸው በዓለማቀፉ አሸባሪ ቡድን በአይሲስ የተገደሉት ኢትዮጵያውያን ሰማዕታትን ለማሰብ የመንበረ መንግሥት (ግቢ) ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ሚያዝያ 23 ቀን 2007 ዓ.ም. ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ አዘጋጅቷል፡፡ በዕለቱ “ሰማዕትነት በዘመናችን” በሚል ዐቢይ ርእስ የምክክር ጉባኤ የሚደረግ ሲኾን ሚያዝያ 20፣ 21፣ እና 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ለሦስት ተከታታይ ቀናት ከቀኑ 12፡00 ሰዓት ዠምሮ የጸሎት መርሐ ግብር ይካሔዳል፡፡

FeedBurner FeedCount