Tuesday, October 13, 2015

የረቡዕ ፍጥረታት



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 2 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ትምህርተ ሃይማኖት - ክፍል ዐሥራ ስድስት
ቸሩ እግዚአብሔር በዚህ በአራተኛው ቀን ሦስት ፍጥረታትን ማለትም፡- ፀሐይን፣ ጨረቃንና ከዋክብትን ፈጥሯል፡፡ የፀሐይ አፈጣጠር ከእሳትና ከነፋስ ሲኾን የጨረቃና የከዋክብት ደግሞ ከውኃና ከነፋስ ነው፡፡
ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ ምናልባት ልንጠይቀው የምንችል ጥያቄ፡- “በመጀመሪያው ቀን ላይ ብርሃን ተፈጥሯል፡፡ ሌላ ብርሃን ታዲያ ለምን አስፈለገ?” በማለት ይጠይቅና እርሱ ራሱ እንዲህ ሲል ይመልስልናል፡- “አስቀድሞ የተፈጠረው የብርሃን ተፈጥሮ ነው፡፡ አሁን ደግሞ ቀድሞ ለተፈጠረው ብርሃን መሣሪያ ትኾን ዘንድ ፀሐይ ተፈጠረች፡፡ ኩራዝ ማለት እሳት ማለት አይደለም፡፡ እሳት የማብራት ባሕርይ አለው፡፡ ኩራዝን የሠራነው ያ እሳት ሥርዓት ባለው መልኩ በጨለማ ላይ እንዲያበራልን ነው፡፡ እነዚህ የብርሃን አካላትም የተፈጠሩት ልክ እንደዚሁ አስቀድሞ የተፈጠረውን ብሩህና ጽሩይ ብርሃን መሣሪያ እንዲኾኑ ነው” /አክሲማሮስ፣ ክፍለ ትምህርት 6 ቍ. 2/፡፡

Sunday, October 11, 2015

ዕለት ዕለት ቃለ እግዚአብሔርን ለማያነቡ ሰዎች የተሰጠ ተግሣፅ



በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 30 ቀን፣ 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ቃለ እግዚአብሔር መንፈሳዊ መሣሪያ ነው፡፡ ይህን መንፈሳዊ መሣሪያ እንዴት እንደምንጠቀምበትና እንደምንታጠቀው ካላወቅንበት ግን በእጃችን ስላለ ብቻ ምንም ሊጠቅመን አይችልም፡፡ ጠንካራ ጥሩርና ራስ ቍር፣ ጋሻና ሰይፍ አለ እንበል፡፡ አንድ ሰው መጥቶም እነዚህን ታጠቃቸው፡፡ ነገር ግን ጥሩሩን በእግሩ፣ ራስ ቍሩን በራሱ ላይ ሳይኾን በዓይኑ ላይ፣ ጋሻውን በደረቱ ላይ ሳይኾን በእግሩ ላይ አሰረው እንበል፡፡ እንግዲህ ይህ ሰው እነዚህን መሣሪያዎች ስለ ታጠቀ ብቻ ጥቅም ያገኛልን? ይባስኑ የሚጎዳ አይደለምን? ይህ ለማንም ግልጽ ነው፡፡ ይህ ሰው ተጠቃሚ ያልኾነው ግን ከመሣሪያው ድክመት አይደለም፤ እንዴት መጠቀም እንዳለበት ሰውዬው ስለማያውቅ እንጂ፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ዘንድም እንደዚህ ነው፡፡ ትእዛዙን በአግባቡ የማንጠቀምበት ከኾነ የቃሉ ኃይል ምንም ባይቀንስም እኛ ግን ምንም የምንጠቀመው ነገር አይኖርም፡፡

Thursday, October 8, 2015

ዘመነ ጽጌ



በዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 27 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ክኅሎቱ ከፍጡራን ኅሊና በላይ የሆነ የቅዱሳን አምላክ የመላው ዓለም ፈጣሪ "ይህን" የሚታየውንና "ያን" የማይታየውን ሁሉ መልካም አድርጎ ፈጥሮታል:: በዚህም ሁሉ ውስጥ ፍጥረታቱ ለመገኘታቸው ሦስት መንገዶች እና ሦስት አላማዎች ታይተዋል:: መንገድ ላልነው በኃልዮ(በማሰብ) የተፈጠሩ አሉ እንደመላእክት ያሉት ለዚህ ምሳሌ ሆነው ይቀርባሉ:: ደግሞም በነቢብ(በመናገር) የተፈጠሩ አሉ እንደ ብርሃን ያሉትን ለአብነት መጥቀስ የሚቻል ሲሆን በሦስተኛው መንገድ በገቢር (በሥራ) የሰውን ልጅ ብቻ ፈጥሮታል:: ለሦስት አላማ ያልነውን ስናይ ደግሞ፡-

Tuesday, October 6, 2015

የማክሰኞ ፍጥረታት



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 25 ቀን 2008 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ትምህርተ ሃይማኖት - ክፍል ዐሥራ አምስት
ሦስተኛይቱ ዕለት ዕለተ ሠሉስ ትባላለች፡፡ ሠሉስ ማለት ለፍጥረት ሦስተኛ ማለት ነው፡፡ በአማርኛ ማግሰኞ ትባላለች፤ የሰኞ ማግስት እንደ ማለት ነው፡፡ በተለምዶ ግን ማክሰኞ እንላለን፡፡ እኛም አንባብያንን ግራ ላለማጋባት በዚህ አካሔድ እንቀጥላለን፡፡
እግዚአብሔር አምላካችን ሰኞ ላይ ውኃዉን ከሦስት ከፍሎ ምድርን ግን ከውኃ እንዳልለያት ተነጋግረን ነበር፡፡ በዚህ ዕለት ማለትም ማክሰኞ ላይ ግን በዚህ ዓለም የነበረውን ውኃ ወደ አንድ ስፍራ እንዲሰበሰብ አድርጓል፡፡ ውኃው ሲሰበሰብም ምድር ተገልጣለች፡፡ ነገር ግን ተገለጠች እንጂ ቡቃያ አልነበረባትም፡፡ በመኾኑም በምሳር የሚቈረጡ (እንደ ዋንዛ፣ ዝግባ፣ ወዘተ)፣ በማጭድ የሚታጨዱ፣ በጥፍር የሚለቀሙ (እንደ ሎሚ፣ እንደ ትርንጎ ያሉ) አዝርእትን፣ አትክልትንና ዕፅዋትን እንድታስገኝ አዘዛት፡፡ ምድርም የቃሉን ትእዛዝ አድምጣ እነዚህን ሦስት ፍጥረታትን አምጣ ወለደች /ዘፍ.1፡12-14/፡፡

FeedBurner FeedCount