Tuesday, October 23, 2012

ከማኻ ዝበለ መሓሪ መን እዩ?


በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን!

ናይዛ ትምህርቲ እዚኣ ቐንዲ ዕላማ ኩላትና ምሕረት ምግባር ንኽንለማመድ ምትብባዕ እዩ፡፡
ነዚኣ ቃል እዚኣ ዝተዛረባ ማኅሌታይ ኣቦና ቅዱስ ያሬድ እዩ፡፡ ቅዱስ ያሬድ ምሕረት እግዚኣብሄር ኣብ ብሉይ ኪዳን ብዕምቆት እንዳስተንተነ የመስግን፤ ይዝምር ከኣ፡፡ ኣስፍሕ ኣቢሉ ክገልፆ እንተሎ “ቃል ኪዳንካ ምስ ኖህ ዘፅናዕካ፣ ንእስራኤላውያን ካብ ሰማይ ማና ኣውሪድካ ዝመገብካ፣ ንምድሪ ጽጌሬዳ ዕንበባን ፍርያትን ሂብካ ፍጥረት ኩሉ እትምግብ፣ ንሰማይን ምድርን ዝፈጠርካ፣ ኩሉ ፍጥረት ብተስፋ ንኣኻ ዝጽበ ከማኻ ዝበለ መሓሪ መን እዩ?” ይብል፡፡ ዋላ ሓደ!

ምሕረት ማለት ቅፅዓት ንዝግብኦ ገበነኛ ርህራሄ ምግባር እዩ /መዝ.51፡1፣7-8/፡፡ ፍቱዋት! ከም ኣበሳና እንተንፍደ ከምቲ ቅፅዓት ዝግበኣና ከኣ እንተንኽፈል ነይርና ኣብ ሓንቲት ሰዓት ጥራይ ክንደይ ጊዜ ምሞትና? እስቲ ካብ ዝወግሕ ጀሚሩ ክሳብ እዛ ሕጂ ዘለናያ ደቒቓ ጥራሕ ክንደይ ግዘ አበስና? እሞ ኣምላኽናኸ ክንደይ ግዘ ሓለፈና? ልቢ ኣምላኽ ዳዊት ነዚ እንዳስተንተነ እንትዝምር ከምዚ ይብል፡- “እግዚኣብሄር ርህሩህን መሓርን እዩ፤ ንኹራ ደንጓዪ፤ ብምሕረት ድማ ምሉእ እዩ፡፡ መግናሕቱ ንግዚኡ እዩ፤ ንዘልኣለም ከኣ ኣይቕየምን እዩ፡፡ ከም መጠን ሓጢኣትና ኣይቀፅዓናን እዩ፤ ከም መጠን አበሳና ድማ ኣይፈድየናን እዩ፡፡ ሰማይ ካብ ምድሪ ልዕል ከም ዝብል ከምኡ ምሕረቱ ኣብ ልዕሊ እቶም ዝፈርሕዎ ዓብዪ እዩ፡፡ ምብራቕ ካብ ምዕራብ ከም ዝርሕቕ ከምኡ ኣበሳና ኻባና ኣርሐቐ” /መዝ.103፡8-12/፡፡ 

እግዚኣብሄር ወልድ ኣብ ደንበ ማል ዝተወልደ፣ ገና ብዕሸሉ እንተሎ ኣብ ሕቑፊ ኣዲኡ ዝተሰደደ፣ በኳሩ እኳ መሕደሪ ጕድጓድ እንዳሃለወን ንሱ ግና ርእሱ ዘፅግዓላ እንተይሃለዎ ከርተት ዝበለ፣ ኣብ መስቀል ዕርቃኑ ወፂኡ ስሌና ዝሓመመን ዝተሳቐየን፣ ብመወዳእትኡ ከኣ ብኣሰቃቒ ሞት ዝሞተ ንዓለም ብምልኡ ምሕረት ክገብረሉ ስለ ዝፈተወ እዩ /ኤፌ.2፡4-5፣ 1ጴጥ.1፡3፣ ሮሜ.5፡6-10/፡፡ ናይ ኣምላኽ ምሕረቱ ካብ ሕሊና ሓሳብ ኩሉ ዝበዝሕ እዩ /ዘኅ.14፡18/፤ ክሳብ ሰማያት ዝበፅሕ ሰፊሕ እዩ

Thursday, October 18, 2012

ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ


  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

 ባለፈው ዝግጅታችን ስለቅዱሳን ሐዋርያት አጠቃላይ መግቢያ አቅርበን በቀጣይነት ደግሞ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የእያንዳንዱን ሐዋርያ የተጋድሎ ሕይወት በዝርዝር እንደምናቀርብ ቃል ገብተን ነበር (የባለፈውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ በመሆኑም ለዛሬ የሐዋርያት አለቃ የሆነውን የሐዋርያው የቅዱስ ጴጥሮስን ሕይወትና ተጋድሎ እነሆ ብለናል መልካም ንባብ።

Tuesday, October 16, 2012

አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ- የዮሐንስ ወንጌል የ 39ኛ ሳምንት ጥናት


(ዮሐ.8፡48-59)

  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ክፋትን የሚሠራት ሰው በጣም የባሰና አሳፋሪ የሚያደርገው ተሸማቅቆና አፍሮ ራሱን መደበቅ ሲገባው ይባስኑ ለስሕተቱና ለክፋቱ ምክንያትን እየፈለገ ሲቀጥልበት ነው፡፡ አይሁዳውያንም እንዲህ ዓይነት ሰዎች ነበሩ፡፡ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እናንተ የአብርሃም ልጆች አይደላችሁም፡፡ የአብርሃምስ ልጆች ብትሆኑ የአብርሃምን ሥራ በሠራችሁ ነበር፤ ከአብ ዘንድ በሕልውና ያየሁትንና የሰማሁትን እውነቱን የምነግራችሁ እኔን ልትገድሉኝ ትሻላችሁና፡፡ አብርሃም እንዲህ አላደረገም፤ ነፍስ አልገደልም፡፡ መግደልስ ይቅርና ልጁን ነበር ለእግዚአብሔር የሠዋው፡፡ ነፍስስ መግደል ይቅርና የወጣው የወረደውን፣ ያለፈው ያገደመውን እንግዳ ነበር ሲቀበል የነበረው፡፡ እንኳንስ እንዲህ ያለ ትምህርት አግኝቶ ነግረውትና አስተምረውት አላምንም ማለት ይቅርና ወጥቶ ወርዶ ነበር ፈጣሪውን ያገኘው፡፡ ስለዚህ እናንተ ልትገድሉኝ እንደምትሹ አባታችን የምትሉት አብርሃም እንዲህ አላደረገም፡፡ በዚያም ላይ ደግሞ ባስተምራችሁ አልተቀበላችሁኝም፡፡ ስለዚህ የአባታችሁኝ የሰይጣን ሥራን ትሠራላችሁና አባታችሁ አብርሃም አይደለም፡፡ እናንተስ ከእግዚአብሔር አይደላችሁም” ብሎ ማየት ያቃታቸውን የመረቀዘ ቁስላቸውን ቢያሳያቸው የባሰ ተናደዱ (ይህን የበለጠ ለማንበብ እዚህይጫኑ)፡፡ በቁስላቸው ላይ ጨው ጨመሩበት፤ “አንተ በእውነት ሳምራዊ ነህ (አይሁዊ አይደለህም) የምንልህ ስለዚሁ አይደለምን? ጋኔን አድሮብሃል፤ የእግዚአብሔር ልጅ አይደለህም የምንልህስ በዚህ ምክንያት አይደለምን?” ብለው ከወገንነት አውጥተው ከይሁዲነት አግልለው ሰደቡት /ቁ.48/፡፡ እንደ እነርሱ አስተሳሰብ ሳምራዊ ማለት የተናቀ፣ የሚለውን የማያውቅና እንዲሁ የሚዘባርቅ፣ ከአይሁድ ጋር የማይተባበር ይልቁንም የአይሁድን እምነት የሚያናንቅ ነው፡፡ በዚህ አነጋገራቸው ጌታችን ጸረ አይሁድ አቋም እንዳለው አስመስለው ለማቅረብም ሞክረዋል፡፡ አይሁድ ሆይ! ጋኔን ያደረበት ማን ነው? እግዚአብሔርን የሚያከብር ወይስ እግዚአብሔር አብን ያከበረው ወልድን የሚሳደብ? /St. John Chrysostom, Homily 55/፡፡


Monday, October 8, 2012

ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ


   በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

የዚህ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያኖች ከጌታችንና ከእመቤታችን ስደት በረከት ተሳታፊዎች እንዲሆኑ ማድረግ ነው፡፡ ቀዳማዊ አዳም የማይበላ በልቶ በራሱና በልጆቹ የሞት ሞት ተፈረደበት፤ ጸጋ እግዚአብሔር ጎደለበት፤ የሚሠዋው መሥዋዕት የሚጸልየው ጸሎት ግዳጅ የማይፈጽም ሆነበት፡፡ ምድር ከእርሱ የተነሣ እሾክና አሜከላ አበቀለችበት፡፡ 

ሆኖም (አዳም) ምንም ባልበደለው ሰይጣን እንዲሁ ቢሞትም የተበደለው አምላኩ ግን እንዲሁ ሕይወትን ይሰጠው ዘንድ ወደደ፡፡ (አዳም) አምላክ መሆንን ሽቶ ነበርና ይህን ይሰጠው ዘንድ (አምላክ) ዳግማይ አዳም ይሆንለት ዘንድ ወደደ፤ አስቀድሞ ከነበረው ክብር በላይ ሌላ ክብር ይጨምርለት ዘንድ ፈቀደ፡፡ ጊዜው ሲደርስም አካላዊ ቃል ንጹሕ የሆነ ባሕርዩን (የእመቤታችን ሥጋና ነፍስ) ነሥቶ ዝቅ ያለውን ከፍ ያደርገው ዘንድ ዝቅ አለለት፤ የጸጋ ልብሱን ይመልስለት ዘንድ የማይዳሰስ እርሱ በጨርቅ ተጠቀለለት፤ ወደ ክብሩ ይመልሰው ዘንድ በርካሽ ቦታ ያውም በግርግም ተወለደለት፡፡

FeedBurner FeedCount