Thursday, February 27, 2014

ዘወረደ ዘዐርብ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
 
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 21 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ
ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ 

 የጽዮን አምሳያ ለሆነችው ቤተክርስቲያን እንዲህ ይላል ቅዱስ አባት ዜመኛው ኢትዮጵያዊጎሕ ጎሐ ወኮነ ጽባሐ ንሳለማ ለጽዮን ምክሐ እምነ በሀ - ሌሊቱ ነጋ ጠዋትም ሆነ መመኪያችን እናታችን ጽዮን እንሳለማት፡፡” እኔም በቤተክርስቲያን ጡቶች ያደግሁ ከእርሷ በሚሆን ወተት ላደጉና ለኖሩ ምዕመናን እናታችን ለምትሆን ለቤተክርስቲያን ዜመኛው በሰጣት ሰላምታ የጽዮን ልጆች ሆይ ሰላም ለእናንተ ይሁን ሰላማችሁ ይብዛ፡፡ ትናንት በቅኔ ማሕሌት እንደተኛው ከበሮ (ከበሮ አገልግሎት በዚህ ወቅት አይሠጥም) ሳይሆን የድካም የሆነ ወዝ (ላብ) ከማይታይበት ከላይ ታች፣ ከግራ ቀኝ፣ ወደፊት ወደኋላ በሚለው መቋሚያ እየታገዝን ዜማውን በቤተክርስቲያን ስለቤተክርስቲያን ሠምተናል፡፡ ዛሬም እንዲሁ ስለ ቅድስት ቤተክርስቲያን (ጽዮን) እና ቅዱስ መስቀል በመሃልም መልካም ቃለ እግዚአብሔር እንሠማለን፣ የአባታችን አምላክ ከመላእክቱ ጋር ያሰልፈን፡፡

Wednesday, February 26, 2014

ዘወረደ ዘሐሙስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 19 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

ወገኖቼ ዛሬ በሐሙስ ዜማችን በእኔ ሳይሆን .ያሬድ ዛሬ ብዙውን ስለሚወራላት ቤተ ክርስቲያ በሰጣት የጅማሬ ሰላምታ በሀክሙ እላችኋለሁ። ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር የሆነ ደስ ያላችሁ ሆይ ደስ ይበላችሁ እላለሁ።

ትናንት በረቡዕ ድርሰቱ ራስን መመርመር፣ ጾምን፣ መገዛትን፣ ምስጋናን፣ መውደድን ፣ የተራበን ማጥገብን፣ ለድሃውም መፍረድን መልካም እንደሆን ነግሮን እነዚህን ሁሉ ደግሞ በጾም ወቅት ማድረጉ የበለጠ ተገቢ ነውና ጾማችንን አብረን ቀድሰን እንድንፈጽም በሰላም መንገድ እንድንጓዝ ብሎን ለዛሬ አቀብሎን ነበረ።

ዘወረደ ዘረቡዕ




በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 18፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

ሰላም ለሁላችሁ ይሁን ። በክርስቶስ ወገኖቼ የሆናችሁ ተወዳጆች በትናንት የማክሰኞ ድርሰቱ አባታችን ቅዱስ ያሬድ በፍቅርና በትህትና እንጹም ብሎ ጀምሮ በጾም ከአለም ልቀን ከፍ ከፍ እንድንል መክሮ ሳይተወን ከፍ ከፍ ማለታችን ደግሞ ምድራዊ ሕዋሳቶቻችንን ሁሉ በማጾም እንደሰማያዊ እንድንሆን ነው ካለን በኋላ በመጨረሻም በክርስቶስ መርቆን ተለያየን። ዛሬ በዕለተ ረቡዕ የሚያዜመውን ከዝማሜው ጋር እንደወትሮው ነፍሳችን ትሰማው ዘንድ እየጸለይን እንቀጥላለን።

ዘወረደ ዘሠሉስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 17 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ
ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ
 አባታችን በትናንት ሰኞ ዘወረደ ድርሰቱ አንዳየነው ከላይ በወረደው በጌታ ስም ጀምሮ በዓለም ታንቀንበት የነበረውን ያለፈውን የኃጢአት ገመድ አላቆ የጾምን ክብር በተለይም የዚህን ጾም ክብር ገልጦልናል።በመጨረሻም ተመለሱ ወደ እርሱም ቅረቡ እርሱም አለም ከሚሰጣችሁ ደስታ የተለየ ደስታ ይሰጣችኋል ብሎን ነበረ። ዛሬ ደግሞ በዛው ነፍሳችን በምትሰማው ሠማያዊ ዜማ የሚለን ነገር አለ።

FeedBurner FeedCount