Wednesday, August 8, 2012

ፍቕሪ እግዚኣብሄርስ…

ሓደ ሓደ ሰባት ኣዳም ካብ ገነት ብምብራሩ ከም ቅፅዓት ጥራሕ ገይሮም ይሓስብዎ፡፡ ኣቦና ቅዱስ ኤፍሬም ወዲ ሶርያ ግና፡- “አዳም ካብ ኤደን ገነት ዝወፅአስ ብፍቕሪ ኣምላኽ እውን ደኣ ‘ምበር በቲ ቕኑዕ ፍርዲ ኣምላኽ ጥራሕ ኣይነበረን” ይብለና፡፡ “ከመይሲ ኣዳም ምስ ኣበሰ ካብ ገነት እንተዘይባረር ነይሩ ምስ ርስሓቱ እንዳሃለወ እታ ናይ ሂወት ኦም ምበልዐ ነበረ፡፡ እዚኣ በልዐ ማለት ከዓ ካብ ርስሓቱ እንተይፀረየ ማለት እውን ምስ ጉድለቱ እንዳሃለወ ናብ መንግሥተ ሰማይ ምኣተወ ነይሩ፡፡ ንዘላኣለም እውን ጐዶሎ ምኾነ ነበረ፡፡ ኮይኑ ግና ጐይታ ኣፅርዩ ከእትዎ ስለ ዝደለየ ክሳብ ባዕሉ መፂኡ ዘፅርዮ በቲ ቅኑዕ ፍትሑ ካብ ገነት አውፅኦ፡፡ ጊዜኡ ምስ በፅሐ ውን ባዕሉ መፂኡ ሥጋኡን ደሙን ናይ ሂወት ኦም ገይሩ ሃቦ’ሞ ነቲ ብልቡ ዝሐዘነ ኣዳም ናብ ናይ ቀደም መንበሪኡ መለሶ” ይብለና!!
እሞ እቲ ፍቕሪ እግዚአብሔርስ ዋላ ኣብቲ ንዓና ሕማቕ ዝመስለና ሃዋህው እውን ምህላዉ ኣየግርምን ዶ ትብሉ?

Tuesday, August 7, 2012

KADHATA


   
Maqaa Abbaa kan Ilmaa kan Afuura Qulqulluu Waaqa Tokko Ameen!
SEENSA
   Kadhata jechuun harka Waaqayyoo irraa eebba gaafachuu jechuu dha. Karaa kan birootiin immoo gatii kadhannaadhaan argamu jechuu dha. Kanaafis ragaan “Isa kadhateef gatiin isaa isaaf laatama” jedha. Gabaabaatti kadhata jechuun Waaqayyo wajjin haasa’u meeshaa wanna feene (barbaanne) tokko Waaqayyo biraa ittiin argannu dha. 
  Kadhata yeroo mara osoo addaan hin kutiin kadhachuun akka nurra jiru; addaan kutuun akka nurra hin jirre yeroo barsiisu Gooftaan fakkeenyaan akkas jedhee isaanitti dubbate kunis Wangeela Luqaas boqonnaa 18 lakk. 1-14 irratti isa barreeffame dha. Kadhannaadhaaf gaggeessaa keenya kan ta’e Gooftaan keenya Iyyesuus Kiristoos iddoo tokkotti kadhannaa taasisee erga xumuree booda barattoota (duukaa buutota) isaa kessaa tokko “Yaa Gooftaa Yohaannis barattoota isaa akkuma kadhannaa barsiise; atis nuun nu barsiisi” isaan jedhe. Gooftaan keenyas deebisee isinis yeroo kadhattan; “Yaa Abbaa keenyaa samii irra kan jiraattu maqaan kee haa galateeffamu; mootummaan kee haa dhufu eeyyamni kee samii irratti akkuma ta’e akkasumas lafa irratti haa ta’u kan nu ga’u soorata keenya (biddeena keenya) har’a nuuf laadhu (kenni) kan nu yakkaniif yakka isaanii akkuma dhiisnu yakka keenya nuuf dhiisi hamaa irraa nu oolchi malee qorumsatti nu hin galchiin.” (Luq. 11: 1-4) jedhee isaan  barsiise. 
  Kanaafuu kiristaana kan ta’e martinuu maqaa Abbaa Ilmaa Afuura Qulqulluutti amanee qaamolee sadan waaqummaadhaan waaqa tokko jedhee yeroo mara kadhannaa gara Uumaa isaatti dhiyeessuu qaba. Kadhannaan abboommii Waaqa biraa ajajame ta’uun isaa kitaaba qulqulluu keessatti iddoo baay’eetti barreeffameera. 
1ffaa - Gooftaan keenyaa fi Fayyisaan kenyaa Iyyesuus Kiristoos  “Qormaatatti akka hin seenneef jabaadhaa kadhadhaa” jedheera. (Maat.26:41)
2ffaa – “Kan kadhattan mara akka argattaniitti taasisaa amanaa isiniif raawwatama. Kadhannaadhaaf yeroo dhaabbattanus Abbaan keessan inni samii gubbaa jiraatu ammoo cubbuu keessan akka isinii dhiisuuf eenyu illee kan isin yakke yoo jiraate dhiifama godhaafi dhiifama gochuufii yoo diddan Abbaan keessanis dhiifama isiniif hin godhu. (Maar. 11:24-26) 
3ffaa – “Onneen keessan baay’ina dhugaatii fi machiin waa’ee gaa’ilaa yaaduun akka hin dadhabne, guyyaan sunis akka tasaa akka isinitti kiyyoo isinirraan ga’u egaa dhufuuf kan jiru kana mara  jalaa miliquuf ilma namaa (Kiristoos) dura dhaabbachuuf akka dandeessanitti yeroo kadhattanu yeroo mara jabaadhaa. (Luq. 21:34-36)
4ffaa – “Dhuguma dhuguman isiniin jedha; Abbaan maqaa kootiin kan isin kadhattanu mara isiniif laata (kenna) hanga yoonaatti maqaa kootiin homaa hin kadhanne gammachuun keessan tasa gaarii akka ta’uuf kadhadhaa ni fudhattu.” (Yoh. 16:24) Duukaa bu’ichi fi Qulqullichi Phaawuloosis “Osoo addaan hin kutiin kadhadhaa” isan jedhe sanas hin dagatiin (1 Tasaloonqee 5:16)
  Egaa gabaabaadhumatti seensa kadhannaaf akka ta’u yaadnee kan barreessine kun kadhannaa isa guddaaf seensa akka ta’uuf yaadnee kadhannaa isa guddaa irraa hir’isnee gabaabsuudhaan Afaan Gi’iiziitiin isa barreeffame mara amantoota Afaan Gi’iizii fi Afaan Amaaraa hin beekneef Afaan Oromoo isa beekaniin yoo kadhatan akkan isaan fayyadu ta’uu isaa yaaduun yeroo mara sa’aatiitiin kadhachuu kan danda’an martinu akka ittiin kadhatanuuf sababa hojiitiin yeroo yerootti kadhachuu namoota hin dandeenyeef sa’aatii mijataa guyyaa boqonnaa akka ittiin kadhatanuuf yeroo gabaabaa keessatti  dubbisamee kan dhumu baay’atee kan hin quufamne kitaaba jaallatamaa waan ta’eef amantoonni martinuu akka itti fayyadamanuuf kitaabni kun qophaa’eera. 
Itti fufa...   
Galanni Waaqayyoof akkasumas Haadhaa fi Giiftii keenya Maariyaamiif haa ta’u Ameen!
( Qopheessaan: Nugusuu Alamuu)

Sunday, August 5, 2012

ነገረ ዕርገት ዘድንግል ማርያም!


    ገ/እግዚአብሔር ኪደ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ ነሐሴ ፲፬ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም)፡- አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ነገረ ዕርገቷን እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ እንናገራለን፡፡

  ተወዳጆች ሆይ! “አቤቱ ወደ ማረፍያህ ተነሥ፤ አንተም የመቅደስህ ታቦትም” እያለ መሰንቆውን ንጽሕት ክብርት ስለምትሆን ስለ ድንግል ማርያም ሲደረድር፣ ሲዘምር፣ ሲያመሰግን ስሙት፡፡ ሁሉም ምሳሌዎች ይገቧታልና ነብያትም መዝሙረኛውን መስለው በብዙ ሕብረ አምሳል አመስግነዋታል፡፡ ፍቁራን ሆይ! ከአዳም ጀምረው እስከ ዛሬ ድረስ በየዘመኑ የተነሡት ሁሉ እንደምን እንደተባበሩ የምንሰማ እንሁን፡፡ ነቢዩ ሰሎሞን “በየትውልዱ በጻድቃን ሕሊና ትመላለሳለች” እንዳለ ሁሉም መዋትያን ቢሆኑም ምስጋናዋ ግን አይሞትም፡፡ ልጇ ወዳጇም ምስጋናዋን በየዕለቱ ያዘጋጃል፤ የወንጌልን መንገድ በሚያቀኑ ልጆቹም ምስጋናዋን በአእምሮአቸው ሹክ ይላቸዋል፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን አምላክ በማሕፀኗ የተሸከመች ናትና፤ ኪሩቤል ሱራፍኤል ዙፋኑን በረዐድና በመንቀጥቀጥ የሚሸከሙትን ሰማያዊ መለኮት በዠርባዋ ያዘለች በክንዷም የታቀፈች ናትና፤ ሰማይና ምድር ከፊቱ የሚሸሹለትን የባሕርይ አምላክ እርሱን ከንፈሮቹን የሳመች ናትና፤ ፍጥረታትን ሁሉ በዝናብ አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ የሚመግበውን እግዚአብሔር ወልድ የድንግልና ጡቶቿን ያጠባች ናትና ብጽዕት፣ ንዕድት፣ ክብርት ነሽ ይሏት ዘንድ ሹክ ይላቸዋል፡፡ አዎ! ሥጋቸውን፣ ነፍሳቸውንና ሕሊናቸውን ከኃጢአት ያነጹት ሰዎች ሁሉ ክብራቸው ከድንግል ማርያም ክብር ጋር አይተካከልምና “ወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ! መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል አንቺ ከሴቶች ሁሉ ተለይተሸ የተባረክሽ ነሽ፤ የማሕፀንሽ ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስም የተባረከ ነው ብሎ እንዳመሰገነሽ እኛም ዋሕድ ቃል እግዚአብሔር ከሥጋሽ ሥጋ፣ ከነፍስሽ ነፍስን ነሥቶ በተዋሕዶ ፍጹም ሰው ሆኗልና ምልዕተ ጸጋ፣ ምልዕተ ክብር፣ ምልዕተ ውዳሴ እመቤታችን ሆይ ደስ ይበልሽ” እያሉ ውዳሴዋን ይናገራሉ፡፡ አስቀድመን እንደተናገርን በቅዱሳን ላይ የቅዱሳን ቅዱስ እግዚአብሔር ያድራል፤ ከእመቤታችን ግን በግልጽ ተወለደ፡፡ ቅዱሳንን ይመግባቸዋል፤ ድንግል ግን ሁሉን የሚመግበውን በጡቶቿ አሳደገችው፡፡ ለቅዱሳን ኃይላቸው እርሱ ነው፤ ድንግል ግን በጀርባዋ አዘለችው፡፡

Thursday, August 2, 2012

ከማን እንማር? በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ!


  የትሕትናን ነገር ከወዴት እንፈልጋት? ከወዴት እናግኛት? ከማንስ እንማራት? ወደ ግብረ ገቦች ከተማ፣ ወደ ቅዱሳኑ በዓት፣ ወደ ተራራዎቹ፣ ወደ ዱር ዋሻው፣ ወደ ጋራውና ሸንተረሩ  እንሂድን? አዎ ወደዚያ እንሂድና የትሕትናን ብዛት፣ የትሕትናን ዋጋ፣ የትሕትናን ክብር ከመነኰሳቱና ከመነኮስያቱ ዘንድ እንመልከታት፤ መመልከት ብቻም ሳይሆን እኛም ገንዘብ እናድርጋት፡፡

  ወደዚያ ስንሄድ ቅዱሳኑ ግማሾቹ የሞቀ ወንበራቸውን (ሥልጣናቸውን)፣ ግማሾቹ የሞቀ ሀብት ንብረታቸውን ትተውና ንቀው ሁለንተናቸውን ዝቅ አድርገው በአለባበሳቸው፣ በአኗኗራቸው፣ በአገልግሎታቸውም ትሕትናን ሲለማመዷት ሲኖሯት እናገኛቸዋለን፡፡

 የትዕቢት ሐሳብ፣ ያማረ ልብስን የመልበስ ሐሳብ፣ የተዋበ ቪላን የመሥራት ሐሳብ፣ ብዙ ሠራተኞችን የማስተዳድር ልቡና እንዲሁም ሌሎች ወደ ትዕቢት የሚወስዱ ነገሮች በእነዚህ ቅዱሳን ዘንድ ቦታ የላቸውም፡፡ እነርሱ ራሳቸው እሳቱን ያቀጣጥላሉ፣ እነርሱ ራሳቸው ምግባቸውን ያበስላሉ፣ እነርሱ ራሳቸውም የመጣውን እንግዳ ያስተናግዳሉ፡፡

 በእነዚህ ቅዱሳን ዘንድ የሚሳደብ የለም የሚሰደብም የለም፤ ትእዛዝ የሚቀበል የለም ትእዛዝ የሚሰጥም የለም፤ ከዚያ ይልቅ ሁሉም አገልጋዮች ናቸው፡፡ የመጣውን እንግዳ እግሩን ለማጠብ ይሽቀዳደማሉ፡፡ ይህን ሲያደርጉም አስቀድመው የሰውዬውን ማንነት አይጠይቁም፡፡ ባርያም ይሁን ጌታም ይሁን በእነርሱ ዘንድ ልዩነት የለውምና፡፡ ሰው መሆኑ በቂያቸው ነውና፡፡ በእነርሱ ዘንድ ታላቅ የለም ታናሽም የለም፡፡ ለምን? ማወቅ ተስኖአቸው ተደነጋግሮአቸው ነውን? በፍጹም! ያንን የሚመለከቱበት ልብ ያንን የሚያደርጉበት ሕሊና ስለሌላቸው እንጂ፡፡ ከእነርሱ አንዱ በጣም ታናሽ ነኝ ብሎ የሚያስብ ከሆነ ሌሎቹ እንደዚያ ታናሽ ነው ብለው አይመለከቱትምና፡፡ እነርሱ ራሳቸው ከእርሱ በታች ታናሽ እንደሆኑ የሚያስቡ ናቸውና፡፡

 ለሁላቸውም አንድ ማዕድ አላቸው፡፡ አገልጋዩም ተገልጋዩም አንድ ዓይነት ምግብ፤ አንድ ዓይነት ልብስ፤ አንድ ዓይነት በዓት፤ አንድ ዓይነት የአኗኗር መርሕ አላቸው፡፡ ትንሹን ሥራ የሚሠራ እርሱ በሁላቸውም ዘንድ ታላቅ ነው፤ የከበረ ነው፡፡ ይህ የእኔ ነው ያም የአንተ ነው የሚባል ነገር አይታወቅም፡፡ ለብዙ ሰዎች መጥፋት ምክንያት ለብዙ ዓለማቀፍ ጦርነቶች መነሻ የሆነው ይህ አገላለጽ (ይህ የእኔ ነው ይህ የአንተ ነው የሚል አገላለጽ) በእነርሱ ዘንድ ቦታ ካጣ ሰነባብቷል፡፡
 አንድ ዓይነት መዓድ፣ አንድ ዓይነት ልብስ፣ አንድ ዓይነት በዓት፣ አንድ ዓይነት የኑሮ መርሕ ስላላቸው ትደነቃላችሁን? ምን ይሄ ብቻ? ልባቸውም አንዲት ናት፤ ነፍሳቸውም አንዲት ናት፡፡ በተፈጥሮ እንዲያ ሆኖ አይደለም፤ በፍቅር ስለተሳሰረ እንጂ፡፡ አንዲት ነፍስ ካለቻቸውስ እንደምን አንዱ የበላይ አንዱ የበታች አድርጎ ሊያስብ ይችላል? አንዲት ነፍስ ለራሷ እኔ የበላይ ነኝ አንቺም የበታች ነሽ ልትል ትችላለችን? በፍጹም!

 በእነዚህ ቅዱሳን ዘንድ ባዕለ ጸጋ የለም ደሀም የለም፤ ክቡር የለም ሕሱርም የለም፡፡ እንዲህ ያለ ነገር ከሌለስ ትዕቢትና ኩራት እንደምን መግቢያ ቀዳዳ ሊያገኙ ይችላሉ? በእውነቱ እነዚህ መነኰሳት መነኰሳይያትም ታናናሾችም ታላላቆችም ናቸው፡፡ ሆኖም ግን አስቀድሜ እንደነገርኳችሁ ይህ ነገር ለእነርሱ አይታያቸውም፡፡ ታናሽ

FeedBurner FeedCount